የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘኁልቁ 22
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘኁልቁ የመጽሐፉ ይዘት

      • ባላቅ፣ እስራኤላውያንን እንዲረግምለት በለዓምን ቀጠረ (1-21)

      • የበለዓም አህያ ተናገረች (22-41)

ዘኁልቁ 22:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 33:48

ዘኁልቁ 22:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 24:9፤ መሳ 11:25

ዘኁልቁ 22:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 15:15፤ ዘዳ 2:25

ዘኁልቁ 22:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 31:7, 8፤ ኢያሱ 13:15, 21

ዘኁልቁ 22:5

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ኤፍራጥስን ወንዝ እንደሚያመለክት ከሁኔታው መረዳት ይቻላል።

  • *

    ወይም “የመሬቱን።”

  • *

    ቃል በቃል “ዓይን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 23:3, 4፤ ኢያሱ 13:22፤ 2ጴጥ 2:15
  • +ዘፍ 13:14, 16

ዘኁልቁ 22:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 23:7፤ ኢያሱ 24:9፤ ነህ 13:1, 2

ዘኁልቁ 22:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ጴጥ 2:15፤ ይሁዳ 11

ዘኁልቁ 22:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:20

ዘኁልቁ 22:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የመሬቱን።”

  • *

    ቃል በቃል “ዓይን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:5, 6፤ 23:7, 11፤ 24:10

ዘኁልቁ 22:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:1-3፤ 22:15, 17፤ ዘዳ 33:29

ዘኁልቁ 22:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 24:13

ዘኁልቁ 22:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:8

ዘኁልቁ 22:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:35፤ 23:11, 12

ዘኁልቁ 22:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ጴጥ 2:15፤ ይሁዳ 11

ዘኁልቁ 22:22

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    8/1/2004፣ ገጽ 27

ዘኁልቁ 22:28

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “የአህያዋን አፍ ከፈተላት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ጴጥ 2:15, 16
  • +ዘኁ 22:32

ዘኁልቁ 22:31

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 6:17

ዘኁልቁ 22:32

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:12፤ 2ጴጥ 2:15, 16

ዘኁልቁ 22:33

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:23, 25, 27

ዘኁልቁ 22:37

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:16, 17፤ 24:10, 11

ዘኁልቁ 22:38

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 23:26፤ 24:13

ዘኁልቁ 22:41

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 23:13, 14

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘኁ. 22:1ዘኁ 33:48
ዘኁ. 22:2ኢያሱ 24:9፤ መሳ 11:25
ዘኁ. 22:3ዘፀ 15:15፤ ዘዳ 2:25
ዘኁ. 22:4ዘኁ 31:7, 8፤ ኢያሱ 13:15, 21
ዘኁ. 22:5ዘዳ 23:3, 4፤ ኢያሱ 13:22፤ 2ጴጥ 2:15
ዘኁ. 22:5ዘፍ 13:14, 16
ዘኁ. 22:6ዘኁ 23:7፤ ኢያሱ 24:9፤ ነህ 13:1, 2
ዘኁ. 22:72ጴጥ 2:15፤ ይሁዳ 11
ዘኁ. 22:9ዘኁ 22:20
ዘኁ. 22:11ዘኁ 22:5, 6፤ 23:7, 11፤ 24:10
ዘኁ. 22:12ዘፍ 12:1-3፤ 22:15, 17፤ ዘዳ 33:29
ዘኁ. 22:18ዘኁ 24:13
ዘኁ. 22:19ዘኁ 22:8
ዘኁ. 22:20ዘኁ 22:35፤ 23:11, 12
ዘኁ. 22:212ጴጥ 2:15፤ ይሁዳ 11
ዘኁ. 22:282ጴጥ 2:15, 16
ዘኁ. 22:28ዘኁ 22:32
ዘኁ. 22:312ነገ 6:17
ዘኁ. 22:32ዘኁ 22:12፤ 2ጴጥ 2:15, 16
ዘኁ. 22:33ዘኁ 22:23, 25, 27
ዘኁ. 22:37ዘኁ 22:16, 17፤ 24:10, 11
ዘኁ. 22:38ዘኁ 23:26፤ 24:13
ዘኁ. 22:41ዘኁ 23:13, 14
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
  • 32
  • 33
  • 34
  • 35
  • 36
  • 37
  • 38
  • 39
  • 40
  • 41
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘኁልቁ 22:1-41

ዘኁልቁ

22 እስራኤላውያንም ከዚያ ተነስተው በመጓዝ ከኢያሪኮ ማዶ በዮርዳኖስ አጠገብ በሚገኘው በሞዓብ በረሃማ ሜዳ ሰፈሩ።+ 2 የሴፎር ልጅ ባላቅ+ እስራኤላውያን በአሞራውያን ላይ ያደረጉትን ሁሉ አየ፤ 3 ሞዓብም ከሕዝቡ ብዛት የተነሳ በጣም ፈራ፤ በእርግጥም ሞዓብ በእስራኤላውያን ምክንያት በፍርሃት ታውኮ ነበር።+ 4 ስለዚህ ሞዓብ የምድያምን+ ሽማግሌዎች “በሬ በሜዳ ላይ ያለን ሣር ጠራርጎ እንደሚበላ ሁሉ ይህም ጉባኤ በዙሪያችን ያለውን ሁሉ ጠራርጎ ያጠፋል” አላቸው።

በዚያን ጊዜ የሴፎር ልጅ ባላቅ የሞዓብ ንጉሥ ነበር። 5 እሱም የቢዖርን ልጅ በለዓምን እንዲጠሩት መልእክተኞችን ላከ፤ በለዓም የሚኖረው በትውልድ አገሩ ባለው ወንዝ* ዳር በምትገኘው በጰቶር ነበር።+ እንዲህም ብለው እንዲነግሩት ላካቸው፦ “ከግብፅ ወጥቶ የመጣ አንድ ሕዝብ አለ። ይኸው የምድሪቱን* ገጽ* ሸፍኗል፤+ ደግሞም መጥቶ አፍንጫዬ ሥር ሰፍሯል። 6 እነሱ ከእኔ ይልቅ ኃያላን ስለሆኑ እባክህ መጥተህ ይህን ሕዝብ እርገምልኝ።+ ምናልባትም ድል አድርጌ ከምድሪቱ ላባርራቸው እችላለሁ፤ ምክንያቱም አንተ የባረክኸው ሁሉ የተባረከ፣ የረገምከውም ሁሉ የተረገመ እንደሚሆን በሚገባ አውቃለሁ።”

7 በመሆኑም የሞዓብ ሽማግሌዎችና የምድያም ሽማግሌዎች ለሟርት የሚከፈለውን ዋጋ ይዘው ወደ በለዓም+ ሄዱ፤ የባላቅንም መልእክት ነገሩት። 8 እሱም “እንግዲህ እዚህ እደሩና ይሖዋ የሚለኝን ማንኛውንም ነገር መልሼ እነግራችኋለሁ” አላቸው። ስለዚህም የሞዓብ መኳንንት በለዓም ዘንድ አደሩ።

9 ከዚያም አምላክ ወደ በለዓም መጥቶ+ “ከአንተ ጋር ያሉት እነዚህ ሰዎች እነማን ናቸው?” አለው። 10 በለዓምም እውነተኛውን አምላክ እንዲህ አለው፦ “የሞዓብ ንጉሥ የሴፎር ልጅ ባላቅ እንዲህ የሚል መልእክት ልኮብኛል፦ 11 ‘ከግብፅ ወጥቶ የመጣው ሕዝብ የምድሪቱን* ገጽ* ሸፍኗል። ስለዚህ መጥተህ እነሱን እርገምልኝ።+ ምናልባትም ድል አድርጌ ከምድሪቱ ላባርራቸው እችላለሁ።’” 12 ሆኖም አምላክ በለዓምን “ከእነሱ ጋር እንዳትሄድ። ሕዝቡ የተባረከ ስለሆነ እንዳትረግመው” አለው።+

13 በለዓም በጠዋት ተነስቶ የባላቅን መኳንንት “ይሖዋ ከእናንተ ጋር እንዳልሄድ ስለከለከለኝ ወደ አገራችሁ ሂዱ” አላቸው። 14 በመሆኑም የሞዓብ መኳንንት ተነስተው ወደ ባላቅ ተመለሱ፤ እንዲህም አሉት፦ “በለዓም ከእኛ ጋር ለመምጣት ፈቃደኛ አልሆነም።”

15 ሆኖም ባላቅ ከበፊቶቹ ይልቅ ቁጥራቸው የበዛና ይበልጥ የተከበሩ ሌሎች መኳንንት እንደገና ላከ። 16 እነሱም ወደ በለዓም መጥተው እንዲህ አሉት፦ “የሴፎር ልጅ ባላቅ እንዲህ ይላል፦ ‘እባክህ ወደ እኔ ከመምጣት ምንም ነገር እንዲያግድህ አትፍቀድ። 17 እኔም ከፍ ያለ ክብር አጎናጽፍሃለሁ፤ የምትለኝንም ሁሉ አደርጋለሁ። ስለሆነም እባክህ መጥተህ ይህን ሕዝብ እርገምልኝ።’” 18 ሆኖም በለዓም ለባላቅ አገልጋዮች እንዲህ የሚል መልስ ሰጣቸው፦ “ባላቅ በብርና በወርቅ የተሞላውን የገዛ ቤቱን ቢሰጠኝ እንኳ ከአምላኬ ከይሖዋ ትእዛዝ ወጥቼ ትንሽም ሆነ ትልቅ ምንም ነገር ማድረግ አልችልም።+ 19 ሆኖም እባካችሁ፣ ይሖዋ ሌላ የሚለኝ ነገር ካለ እንዳውቅ ዛሬም እዚህ እደሩ።”+

20 ከዚያም አምላክ በሌሊት ወደ በለዓም መጥቶ እንዲህ አለው፦ “እነዚህ ሰዎች የመጡት አንተን ለመጥራት ከሆነ አብረሃቸው ሂድ። ይሁንና የምትናገረው እኔ የምልህን ብቻ ነው።”+ 21 ስለዚህ በለዓም በጠዋት ተነስቶ አህያውን ከጫነ በኋላ ከሞዓብ መኳንንት ጋር ሄደ።+

22 ይሁን እንጂ በለዓም ጉዞ በመጀመሩ የአምላክ ቁጣ ነደደ፤ የይሖዋም መልአክ በለዓምን ሊቃወመው መንገዱ ላይ ቆመ። በዚህ ጊዜ በለዓም በአህያው ላይ ተቀምጦ እየተጓዘ ነበር፤ ሁለት አገልጋዮቹም አብረውት ነበሩ። 23 አህያዋም የይሖዋ መልአክ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ መንገዱ ላይ መቆሙን ስታይ ከመንገዱ ወጥታ ወደ እርሻ ለመግባት ሞከረች። ሆኖም በለዓም አህያዋን ወደ መንገዱ ለመመለስ ይደበድባት ጀመር። 24 ከዚያም የይሖዋ መልአክ በዚህም በዚያም በኩል በግንብ በታጠሩ ሁለት የወይን እርሻዎች መካከል በሚገኝ ጠባብ መንገድ ላይ ቆመ። 25 አህያዋም የይሖዋን መልአክ ስታይ ግንቡን መታከክ ጀመረች፤ የበለዓምንም እግር ከግንቡ ጋር አጣበቀችው፤ በለዓምም እንደገና ይደበድባት ጀመር።

26 የይሖዋም መልአክ እንደገና አልፎ ወደ ቀኝም ሆነ ወደ ግራ መፈናፈን በማያስችል ጠባብ ቦታ ላይ ቆመ። 27 አህያዋም የይሖዋን መልአክ ስታይ በለዓም ላይዋ ላይ እንዳለ ተኛች፤ በዚህ ጊዜ በለዓም እጅግ ተቆጣ፤ አህያዋንም በዱላው ይቀጠቅጣት ጀመር። 28 በመጨረሻም ይሖዋ አህያዋ እንድትናገር አደረገ፤*+ እሷም በለዓምን “ሦስት ጊዜ እንዲህ የመታኸኝ ምን አድርጌህ ነው?”+ አለችው። 29 በለዓምም አህያዋን “ስለተጫወትሽብኝ ነዋ! በእጄ ሰይፍ ይዤ ቢሆንማ ኖሮ እገድልሽ ነበር!” አላት። 30 ከዚያም አህያዋ በለዓምን “እስከ ዛሬ ድረስ በሕይወትህ ሙሉ የተቀመጥክብኝ አህያህ አይደለሁም? ከዚህ በፊት እንዲህ አድርጌህ አውቃለሁ?” አለችው። እሱም “በጭራሽ!” አላት። 31 ከዚያም ይሖዋ የበለዓምን ዓይኖች ገለጠ፤+ እሱም የይሖዋ መልአክ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ መንገዱ ላይ ቆሞ አየ። ወዲያውኑም በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደ።

32 ከዚያም የይሖዋ መልአክ እንዲህ አለው፦ “አህያህን ሦስት ጊዜ እንዲህ አድርገህ የመታሃት ለምንድን ነው? መንገድህ ከፈቃዴ ጋር ስለሚቃረን እኔ ራሴ ከጉዞህ ልገታህ መጥቻለሁ።+ 33 አህያዋ አይታኝ ሦስቱንም ጊዜ ከፊቴ ዞር ለማለት ሞከረች።+ እሷ ከፊቴ ዞር ባትልማ ኖሮ ምን ይከሰት እንደነበር አስብ! ይሄን ጊዜ አንተን ገድዬህ አህያዋን በሕይወት በተውኳት ነበር።” 34 በዚህ ጊዜ በለዓም የይሖዋን መልአክ እንዲህ አለው፦ “ኃጢአት ሠርቻለሁ፤ ምክንያቱም አንተ እኔን ለማግኘት መንገድ ላይ እንደቆምክ አላወቅኩም ነበር። አሁንም ቢሆን መሄዴ ጥሩ መስሎ ካልታየህ እመለሳለሁ።” 35 ሆኖም የይሖዋ መልአክ በለዓምን “ከሰዎቹ ጋር መሄዱን እንኳ ሂድ፤ የምትናገረው ግን እኔ የምልህን ብቻ ነው” አለው። በመሆኑም በለዓም ከባላቅ መኳንንት ጋር ጉዞውን ቀጠለ።

36 ባላቅ የበለዓምን መምጣት ሲሰማ በክልሉ ወሰን ላይ በሚገኘው በአርኖን ዳርቻ ባለው በሞዓብ ከተማ ሊቀበለው ወዲያውኑ ወጣ። 37 ባላቅም በለዓምን እንዲህ አለው፦ “እንድትመጣ ልኬብህ አልነበረም? ታዲያ ወደ እኔ ያልመጣኸው ለምንድን ነው? ለመሆኑ እኔ አንተን ታላቅ ክብር ማጎናጸፍ የሚያቅተኝ ይመስልሃል?”+ 38 በለዓምም ባላቅን እንዲህ አለው፦ “ይኸው አሁን ወደ አንተ መጥቻለሁ። ይሁንና ያሻኝን መናገር የምችል ይመስልሃል? እኔ መናገር የምችለው አምላክ በአፌ ላይ የሚያደርገውን ቃል ብቻ ነው።”+

39 በመሆኑም በለዓም ከባላቅ ጋር ሄደ፤ ወደ ቂርያትሁጾትም መጡ። 40 ባላቅም ከብቶችንና በጎችን ሠዋ፤ የተወሰነውንም ለበለዓምና ከእሱ ጋር ለነበሩት መኳንንት ላከ። 41 ጠዋት ላይም ባላቅ በለዓምን ይዞት ወደ ባሞትበዓል ወጣ፤ እዚያ ሆኖ ሕዝቡን ሁሉ ማየት ይችል ነበር።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ