የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘኁልቁ 23
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘኁልቁ የመጽሐፉ ይዘት

      • የመጀመሪያው የበለዓም ምሳሌያዊ አነጋገር (1-12)

      • ሁለተኛው የበለዓም ምሳሌያዊ አነጋገር (13-30)

ዘኁልቁ 23:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:41

ዘኁልቁ 23:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 23:13, 14, 28-30

ዘኁልቁ 23:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:20

ዘኁልቁ 23:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:35

ዘኁልቁ 23:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 23:18፤ 24:3
  • +ዘፍ 10:22፤ ዘኁ 22:5፤ ዘዳ 23:3, 4
  • +ዘኁ 22:6

ዘኁልቁ 23:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:12

ዘኁልቁ 23:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 8:53
  • +ዘፀ 33:16

ዘኁልቁ 23:10

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴ የቅኖች ዓይነት አሟሟት ትሙት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 13:14, 16፤ 22:17፤ ዘፀ 1:7

ዘኁልቁ 23:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 24:10፤ ኢያሱ 24:10፤ ነህ 13:1, 2

ዘኁልቁ 23:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:38፤ 24:13

ዘኁልቁ 23:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:11

ዘኁልቁ 23:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 34:1
  • +ዘኁ 22:41፤ 23:1, 28, 29

ዘኁልቁ 23:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:35፤ 23:5

ዘኁልቁ 23:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 23:7፤ 24:3

ዘኁልቁ 23:19

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “አይጸጸትም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 89:35፤ ቲቶ 1:2
  • +1ሳሙ 15:29
  • +ኢሳ 14:24፤ 46:10፤ ሚክ 7:20

ዘኁልቁ 23:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:1, 2፤ 22:15, 17፤ ዘኁ 22:12
  • +ዘኁ 22:18

ዘኁልቁ 23:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 13:21፤ 23:20፤ 29:45፤ ኢሳ 8:10

ዘኁልቁ 23:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 20:2
  • +ዘኁ 24:8

ዘኁልቁ 23:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 12:1, 3
  • +ዘኁ 22:7

ዘኁልቁ 23:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 24:9

ዘኁልቁ 23:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:38፤ 23:12

ዘኁልቁ 23:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 23:13

ዘኁልቁ 23:28

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “በረሃውን፤ ምድረ በዳውን” ማለትም ሊሆን ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 21:20

ዘኁልቁ 23:29

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 22:41፤ 23:1, 14

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘኁ. 23:1ዘኁ 22:41
ዘኁ. 23:2ዘኁ 23:13, 14, 28-30
ዘኁ. 23:4ዘኁ 22:20
ዘኁ. 23:5ዘኁ 22:35
ዘኁ. 23:7ዘኁ 23:18፤ 24:3
ዘኁ. 23:7ዘፍ 10:22፤ ዘኁ 22:5፤ ዘዳ 23:3, 4
ዘኁ. 23:7ዘኁ 22:6
ዘኁ. 23:8ዘኁ 22:12
ዘኁ. 23:91ነገ 8:53
ዘኁ. 23:9ዘፀ 33:16
ዘኁ. 23:10ዘፍ 13:14, 16፤ 22:17፤ ዘፀ 1:7
ዘኁ. 23:11ዘኁ 24:10፤ ኢያሱ 24:10፤ ነህ 13:1, 2
ዘኁ. 23:12ዘኁ 22:38፤ 24:13
ዘኁ. 23:13ዘኁ 22:11
ዘኁ. 23:14ዘዳ 34:1
ዘኁ. 23:14ዘኁ 22:41፤ 23:1, 28, 29
ዘኁ. 23:16ዘኁ 22:35፤ 23:5
ዘኁ. 23:18ዘኁ 23:7፤ 24:3
ዘኁ. 23:19መዝ 89:35፤ ቲቶ 1:2
ዘኁ. 23:191ሳሙ 15:29
ዘኁ. 23:19ኢሳ 14:24፤ 46:10፤ ሚክ 7:20
ዘኁ. 23:20ዘፍ 12:1, 2፤ 22:15, 17፤ ዘኁ 22:12
ዘኁ. 23:20ዘኁ 22:18
ዘኁ. 23:21ዘፀ 13:21፤ 23:20፤ 29:45፤ ኢሳ 8:10
ዘኁ. 23:22ዘፀ 20:2
ዘኁ. 23:22ዘኁ 24:8
ዘኁ. 23:23ዘፍ 12:1, 3
ዘኁ. 23:23ዘኁ 22:7
ዘኁ. 23:24ዘኁ 24:9
ዘኁ. 23:26ዘኁ 22:38፤ 23:12
ዘኁ. 23:27ዘኁ 23:13
ዘኁ. 23:28ዘኁ 21:20
ዘኁ. 23:29ዘኁ 22:41፤ 23:1, 14
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘኁልቁ 23:1-30

ዘኁልቁ

23 ከዚያም በለዓም ባላቅን “እዚህ ቦታ ላይ ሰባት መሠዊያዎች ሥራልኝ፤+ እንዲሁም ሰባት በሬዎችና ሰባት አውራ በጎች አዘጋጅልኝ” አለው። 2 ባላቅም ወዲያውኑ በለዓም እንዳለው አደረገ። ባላቅና በለዓም በእያንዳንዱ መሠዊያ ላይ አንድ በሬና አንድ አውራ በግ አቀረቡ።+ 3 ከዚያም በለዓም ባላቅን እንዲህ አለው፦ “አንተ እዚህ የሚቃጠለው መባህ አጠገብ ቆይ፤ እኔ ግን ልሂድ። ምናልባት ይሖዋ ይገለጥልኝ ይሆናል። እሱ የሚገልጥልኝን ማንኛውንም ነገር እነግርሃለሁ።” በመሆኑም በለዓም ወደ አንድ ገላጣ ኮረብታ ሄደ።

4 በለዓምም ከአምላክ ጋር በተገናኘ ጊዜ+ “ሰባቱን መሠዊያዎች በመደዳ አቁሜያቸዋለሁ፤ በእያንዳንዱም መሠዊያ ላይ አንድ በሬና አንድ አውራ በግ አቅርቤያለሁ” አለው። 5 ይሖዋም በበለዓም አፍ ላይ ይህን ቃል አስቀመጠ፦+ “ወደ ባላቅ ተመለስና እንዲህ ብለህ ንገረው።” 6 በመሆኑም በለዓም ተመለሰ፤ እሱም ባላቅን ከሞዓብ መኳንንት ሁሉ ጋር በሚቃጠለው መባው አጠገብ ቆሞ አየው። 7 ከዚያም ይህን ምሳሌያዊ አባባል ተናገረ፦+

“የሞዓብ ንጉሥ ባላቅ ከአራም፣+

ከምሥራቅ ተራሮች አመጣኝ፤

‘ና፣ ያዕቆብን እርገምልኝ።

አዎ ና፣ እስራኤልን አውግዝልኝ’ አለኝ።+

 8 አምላክ ያልረገመውን እኔ እንዴት ልረግም እችላለሁ?

ይሖዋ ያላወገዘውንስ እኔ እንዴት ላወግዝ እችላለሁ?+

 9 ከዓለቶቹ አናት ላይ ሆኜ አያቸዋለሁ፤

ከኮረብቶቹም ላይ ሆኜ እመለከታቸዋለሁ።

በዚያ እንደ አንድ ሕዝብ ብቻቸውን ሰፍረዋል፤+

ከሌሎች ብሔራት እንደ አንዱ አድርገው ራሳቸውን አይቆጥሩም።+

10 ከብዛቱ የተነሳ እንደ አፈር የሆነውን ያዕቆብን ማን ሊቆጥረው ይችላል?+

የእስራኤልንስ ሩብ ማን ይቆጥረዋል?

የቅኖች ዓይነት አሟሟት ልሙት፤*

መጨረሻዬም እንደ እነሱ ይሁን።”

11 ባላቅም በለዓምን እንዲህ አለው፦ “እንዴት እንዲህ ታደርገኛለህ? እኔ እኮ ያመጣሁህ ጠላቶቼን እንድትረግምልኝ ነው፤ አንተ ግን ባረክሃቸው እንጂ ምንም አልፈየድክልኝም።”+ 12 እሱም መልሶ “እኔ መናገር ያለብኝ ይሖዋ በአፌ ላይ ያስቀመጠውን ብቻ አይደለም?” አለ።+

13 ከዚያም ባላቅ እንዲህ አለው፦ “እባክህ፣ እነሱን ማየት ወደምትችልበት ሌላ ቦታ አብረን እንሂድ። እርግጥ ሁሉንም አታያቸውም፤ የምታያቸው በከፊል ብቻ ነው። እዚያ ሆነህ እርገምልኝ።”+ 14 እሱም በጲስጋ አናት+ ላይ ወደሚገኘው የጾፊም ሜዳ ወሰደው፤ በዚያም ሰባት መሠዊያዎችን ሠርቶ በእያንዳንዱ መሠዊያ ላይ አንድ በሬና አንድ አውራ በግ አቀረበ።+ 15 በለዓምም ባላቅን “እኔ ከእሱ ጋር ለመገናኘት ወደዚያ ስሄድ አንተ እዚሁ የሚቃጠለው መባህ አጠገብ ቆይ” አለው። 16 ይሖዋም ከበለዓም ጋር ተገናኘ፤ በአፉም ላይ ይህን ቃል አስቀመጠ፦+ “ወደ ባላቅ ተመለስና እንዲህ ብለህ ንገረው።” 17 በመሆኑም በለዓም ወደ ባላቅ ተመለሰ፤ ባላቅንም በሚቃጠለው መባው አጠገብ ሲጠብቀው አገኘው፤ የሞዓብ መኳንንትም ከእሱ ጋር ነበሩ። ከዚያም ባላቅ “ለመሆኑ ይሖዋ ምን አለ?” ሲል ጠየቀው። 18 በለዓምም ይህን ምሳሌያዊ አባባል ተናገረ፦+

“ባላቅ ተነስ፤ አዳምጥ።

የሴፎር ልጅ ሆይ፣ ጆሮህን ስጠኝ።

19 አምላክ እንደ ሰው አይዋሽም፤+

እንደ ሰው ልጅም ሐሳቡን አይለውጥም።*+

እሱ ያለውን አያደርገውም?

የተናገረውንስ አይፈጽመውም?+

20 እንግዲህ የእኔ ተልእኮ መባረክ ነው፤

እሱ እንደሆነ ባርኳል፤+ እኔ ደግሞ ልለውጠው አልችልም።+

21 ያዕቆብን ለማጥቃት የታሰበን ማንኛውንም አስማታዊ ኃይል ዝም ብሎ አያልፍም፤

በእስራኤል ላይ ምንም ዓይነት ችግር እንዲደርስ አይፈቅድም።

አምላኩ ይሖዋ ከእነሱ ጋር ነው፤+

በመካከላቸውም እንደ ንጉሥ ከፍ ባለ ድምፅ ይወደሳል።

22 አምላክ ከግብፅ አውጥቷቸዋል።+

እሱም ለእነሱ ልክ እንደ ጎሽ ቀንዶች ነው።+

23 በያዕቆብ ላይ የሚሠራ ምንም ዓይነት ድግምት የለምና፤+

በእስራኤልም ላይ የሚሠራ ምንም ዓይነት ሟርት የለም።+

በዚህ ጊዜ ስለ ያዕቆብና ስለ እስራኤል

‘አምላክ ያደረገውን ተመልከቱ!’ ይባላል።

24 ልክ እንደ አንበሳ የሚነሳው ሕዝብ ይህ ነው፤

እሱም እንደ አንበሳ ተነስቶ ይቆማል።+

ያደነውን እስኪበላ፣

የተገደሉትንም ደማቸውን እስኪጠጣ ድረስ አይተኛም።”

25 ከዚያም ባላቅ በለዓምን “እንግዲያው ልትረግመው ካልቻልክ ልትባርከውም አይገባም” አለው። 26 በለዓምም መልሶ ባላቅን “‘እኔ የማደርገው ይሖዋ የሚናገረውን ብቻ ነው’ ብዬህ አልነበረም?” አለው።+

27 ባላቅም በለዓምን እንዲህ አለው፦ “እባክህ ና፤ እስቲ አሁንም ወደ ሌላ ቦታ ልውሰድህ። ምናልባትም እውነተኛው አምላክ እዚያ ሆነህ እሱን እንድትረግምልኝ ይፈቅድ ይሆናል።”+ 28 ስለዚህ ባላቅ በለዓምን፣ የሺሞንን* ፊት ለፊት ማየት ወደሚቻልበት ወደ ፌጎር አናት ወሰደው።+ 29 ከዚያም በለዓም ባላቅን “እዚህ ቦታ ላይ ሰባት መሠዊያዎች ሥራልኝ፤ እንዲሁም ሰባት በሬዎችና ሰባት አውራ በጎች አዘጋጅልኝ” አለው።+ 30 ባላቅም በለዓም እንዳለው አደረገ፤ ከዚያም በእያንዳንዱ መሠዊያ ላይ አንድ በሬና አንድ አውራ በግ አቀረበ።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ