ሰቆቃወ ኤርምያስ
א [አሌፍ]
2 ይሖዋ የጽዮንን ሴት ልጅ በቁጣው ደመና እንዴት ሸፈናት!
የእስራኤልን ውበት ከሰማይ ወደ ምድር ጥሏል።+
በቁጣው ቀን የእግሩን ማሳረፊያ አላስታወሰም።+
ב [ቤት]
2 ይሖዋ የያዕቆብን መኖሪያዎች በሙሉ ያላንዳች ርኅራኄ ውጧል።
የይሁዳን ሴት ልጅ የተመሸጉ ቦታዎች በቁጣው አፈራርሷል።+
መንግሥቱንና መኳንንቷን ወደ መሬት ጥሏል፤ ደግሞም አርክሷል።+
ג [ጊሜል]
3 የእስራኤልን ብርታት* ሁሉ በታላቅ ቁጣ ቆረጠ።
ד [ዳሌት]
በጽዮን ሴት ልጅ ድንኳንም ላይ+ ቁጣውን እንደ እሳት አፈሰሰ።+
ה [ሄ]
5 ይሖዋ እንደ ጠላት ሆነ፤+
እስራኤልን ዋጠ።
ማማዎቿን ሁሉ ዋጠ፤
የተመሸጉ ስፍራዎቿን ሁሉ አወደመ።
በይሁዳ ሴት ልጅ ዘንድ ለቅሶንና ዋይታን አበዛ።
ו [ዋው]
6 የራሱን ዳስ በአትክልት ቦታ እንዳለች ጎጆ አፈረሰ።+
ይሖዋ በጽዮን፣ በዓልና ሰንበት እንዲረሳ አድርጓል፤
በኃይለኛ ቁጣውም ንጉሡንና ካህኑን አቃሏል።+
ז [ዛየን]
7 ይሖዋ መሠዊያውን ናቀ፤
መቅደሱን ተወ።+
የማይደፈሩ ማማዎቿን ግንቦች ለጠላት አሳልፎ ሰጠ።+
በበዓል ቀን እንደሚደረገው ሁሉ በይሖዋ ቤት በታላቅ ድምፅ ጮኹ።+
ח [ኼት]
8 ይሖዋ የጽዮንን ሴት ልጅ ቅጥር ለማፍረስ ቆርጧል።+
የመለኪያ ገመዱን ዘርግቷል።+
ከማጥፋትም እጁን አልመለሰም።
የመከላከያ ግንቡና ቅጥሩ እንዲያዝኑ አደረገ።
በአንድነትም ደከሙ።
ט [ቴት]
9 በሮቿ ወደ መሬት ሰጠሙ።+
መቀርቀሪያዎቿን አስወገደ፤ ደግሞም ሰባበረ።
ንጉሥዋና መኳንንቷ በብሔራት መካከል ናቸው።+
ሕግ* የለም፤ ነቢያቷም እንኳ ከይሖዋ የተገለጠላቸው ራእይ የለም።+
י [ዮድ]
10 የጽዮን ሴት ልጅ ሽማግሌዎች ዝም ብለው መሬት ላይ ይቀመጣሉ።+
በራሳቸው ላይ አቧራ ይነሰንሳሉ፤ ማቅም ይለብሳሉ።+
የኢየሩሳሌም ደናግል ራሳቸውን ወደ መሬት ደፍተዋል።
כ [ካፍ]
11 ከማልቀሴ ብዛት ዓይኖቼ ፈዘዙ።+
አንጀቴ ተላወሰ።
ל [ላሜድ]
12 ልክ እንደቆሰለ ሰው በከተማዋ አደባባዮች ተዝለፍልፈው ሲወድቁና
מ [ሜም]
13 የኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ሆይ፣ ምሥክር የሚሆን ምን ነገር ላቀርብልሽ እችላለሁ?
ከምንስ ጋር ላመሳስልሽ እችላለሁ?
ድንግሊቱ የጽዮን ሴት ልጅ ሆይ፣ አጽናናሽ ዘንድ ከማን ጋር ላወዳድርሽ እችላለሁ?
የደረሰብሽ ጥፋት እንደ ባሕር ሰፊ ነውና።+ ማን ሊፈውስሽ ይችላል?+
נ [ኑን]
14 ነቢያትሽ ያዩልሽ ራእይ ሐሰትና ከንቱ ነው፤+
ተማርከሽ እንዳትወሰጂ ለማድረግ በደልሽን አላጋለጡም፤+
ይልቁንም ራእይ ተገለጠልን እያሉ ሐሰትና አሳሳች ቃል ይነግሩሻል።+
ס [ሳሜኽ]
15 በመንገድ የሚያልፉ ሁሉ በማሾፍ እጃቸውን ያጨበጭቡብሻል።+
“‘ፍጹም ውበት የተላበሰችና የምድር ሁሉ ደስታ’+ በማለት ይጠሯት የነበረችው ከተማ ይህች ናት?” እያሉ በመገረም
በኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ላይ ያፏጫሉ፤+ ራሳቸውንም ይነቀንቃሉ።
פ [ፔ]
16 ጠላቶችሽ ሁሉ በአንቺ ላይ አፋቸውን ከፍተዋል።
እነሱ ያፏጫሉ፤ ጥርሳቸውንም ያፋጫሉ፤
ደግሞም “ዋጥናት።+ ስንጠብቀው የነበረው ቀን ይህ ነው!+ ጊዜው ደርሶ ለማየት በቃን!”+ ይላሉ።
ע [አይን]
ያላንዳች ርኅራኄ አፍርሷል።+
ጠላት በአንቺ ላይ በደረሰው ነገር ደስ እንዲሰኝ፣ የባላጋራዎችሽም ብርታት* ከፍ ከፍ እንዲል አድርጓል።
צ [ጻዴ]
18 የጽዮን ሴት ልጅ ቅጥር ሆይ፣ ልባቸው ወደ ይሖዋ ይጮኻል።
እንባሽ እንደ ጅረት ቀን ከሌት ይፍሰስ።
ለራስሽ ፋታ አትስጪ፤ ዓይንሽ እንባ ማፍሰሱን አያቋርጥ።*
ק [ኮፍ]
19 ተነሺ! ሌሊት፣ ክፍለ ሌሊቶቹ ሲጀምሩ ጩኺ።
በይሖዋ ፊት ልብሽን እንደ ውኃ አፍስሺ።
ר [ረሽ]
20 ይሖዋ ሆይ፣ ክፉኛ የቀጣኸውን እይ፤ ደግሞም ተመልከት።
ש [ሺን]
21 ወንድ ልጅና ሽማግሌ ሞተው በየመንገዱ ተዘርረዋል።+
በቁጣህ ቀን ገደልክ፤ ያላንዳች ርኅራኄ አረድክ።+
ת [ታው]
22 በበዓል ቀን እንደሚደረገው ሁሉ+ ሽብርን ከየአቅጣጫው ጠራህ።