የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኤርምያስ 48
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኤርምያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • በሞዓብ ላይ የተነገረ ትንቢት (1-47)

ኤርምያስ 48:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 19:36, 37፤ ኢሳ 15:1
  • +ዘኁ 32:37, 38
  • +ኢያሱ 13:15, 19፤ ሕዝ 25:9
  • +ኢሳ 15:2

ኤርምያስ 48:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 32:37፤ ኢሳ 16:8

ኤርምያስ 48:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 15:5፤ ኤር 48:34

ኤርምያስ 48:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 15:5

ኤርምያስ 48:6

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሳችሁን አትርፉ!”

ኤርምያስ 48:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 21:29፤ 1ነገ 11:7

ኤርምያስ 48:8

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ረባዳማው ሜዳ።”

  • *

    ወይም “አምባውም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 25:9

ኤርምያስ 48:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሶፎ 2:9

ኤርምያስ 48:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 12:28, 29፤ ሆሴዕ 10:15፤ አሞጽ 5:5

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የስብሰባው አስተዋጽኦ የማመሣከሪያ ጽሑፎች፣ 5/2017፣ ገጽ 3

ኤርምያስ 48:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 16:6

ኤርምያስ 48:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 24:8
  • +ኤር 48:8
  • +ኢሳ 34:2

ኤርምያስ 48:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 25:11

ኤርምያስ 48:18

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “በደረቅ መሬትም” ማለትም ሊሆን ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 21:30፤ ኢያሱ 13:15, 17፤ ኢሳ 15:2
  • +ኤር 48:8

ኤርምያስ 48:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 32:34፤ ዘዳ 2:36

ኤርምያስ 48:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 21:13፤ ኢያሱ 13:8, 9

ኤርምያስ 48:21

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ወደ አምባው።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሶፎ 2:9
  • +ዘኁ 21:23፤ ኢሳ 15:4
  • +ኢያሱ 13:15, 18

ኤርምያስ 48:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 32:34
  • +ዘኁ 32:3, 4

ኤርምያስ 48:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 32:37፤ ኤር 48:1
  • +ዘኁ 32:37, 38፤ ኢያሱ 13:15, 17፤ ሕዝ 25:9

ኤርምያስ 48:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +አሞጽ 2:2

ኤርምያስ 48:25

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ቀንድ።”

ኤርምያስ 48:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 48:42
  • +ኤር 25:15, 16

ኤርምያስ 48:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሰቆ 2:15፤ ሶፎ 2:8

ኤርምያስ 48:29

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 16:6፤ 25:10, 11፤ ሶፎ 2:9, 10

ኤርምያስ 48:31

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 3:24, 25፤ ኢሳ 16:7

ኤርምያስ 48:32

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    የበጋ ፍሬ በዋነኝነት የሚያመለክተው “በለስን” ሲሆን “ቴምርንም” ሊጨምር ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 32:37, 38፤ ኢያሱ 13:15, 19
  • +ዘኁ 21:32፤ 32:34, 35፤ ኢያሱ 21:8, 39
  • +ኢሳ 16:8, 9፤ ኤር 48:8

ኤርምያስ 48:33

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 25:10
  • +ኢሳ 16:10

ኤርምያስ 48:34

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 21:25፤ ኢያሱ 13:15, 17
  • +ዘኁ 32:37፤ ኢሳ 16:9
  • +ዘኁ 21:23
  • +ኤር 48:2, 3
  • +ኢሳ 15:4-6

ኤርምያስ 48:36

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    በቀብር ጊዜ ሐዘናቸውን ለመግለጽ የሚጫወቱትን ዋሽንት ያመለክታል።

  • *

    ወይም “ይጮኻል።”

  • *

    በቀብር ጊዜ ሐዘናቸውን ለመግለጽ የሚጫወቱትን ዋሽንት ያመለክታል።

  • *

    ወይም “ይጮኻል።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 16:11

ኤርምያስ 48:37

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 16:6
  • +ዘሌ 19:28
  • +ዘፍ 37:34፤ ኢሳ 15:2, 3

ኤርምያስ 48:40

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሰቆ 4:19፤ ዕን 1:8
  • +ኤር 49:22

ኤርምያስ 48:42

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 30:11
  • +ኤር 48:29

ኤርምያስ 48:45

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 21:26, 28
  • +ዘኁ 24:17፤ አሞጽ 2:2

ኤርምያስ 48:46

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 21:29፤ 1ነገ 11:7
  • +ኤር 48:7

ኤርምያስ 48:47

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 25:11

ተዛማጅ ሐሳብ

ኤር. 48:1ዘፍ 19:36, 37፤ ኢሳ 15:1
ኤር. 48:1ዘኁ 32:37, 38
ኤር. 48:1ኢያሱ 13:15, 19፤ ሕዝ 25:9
ኤር. 48:1ኢሳ 15:2
ኤር. 48:2ዘኁ 32:37፤ ኢሳ 16:8
ኤር. 48:3ኢሳ 15:5፤ ኤር 48:34
ኤር. 48:5ኢሳ 15:5
ኤር. 48:7ዘኁ 21:29፤ 1ነገ 11:7
ኤር. 48:8ሕዝ 25:9
ኤር. 48:9ሶፎ 2:9
ኤር. 48:131ነገ 12:28, 29፤ ሆሴዕ 10:15፤ አሞጽ 5:5
ኤር. 48:14ኢሳ 16:6
ኤር. 48:15መዝ 24:8
ኤር. 48:15ኤር 48:8
ኤር. 48:15ኢሳ 34:2
ኤር. 48:16ሕዝ 25:11
ኤር. 48:18ዘኁ 21:30፤ ኢያሱ 13:15, 17፤ ኢሳ 15:2
ኤር. 48:18ኤር 48:8
ኤር. 48:19ዘኁ 32:34፤ ዘዳ 2:36
ኤር. 48:20ዘኁ 21:13፤ ኢያሱ 13:8, 9
ኤር. 48:21ሶፎ 2:9
ኤር. 48:21ዘኁ 21:23፤ ኢሳ 15:4
ኤር. 48:21ኢያሱ 13:15, 18
ኤር. 48:22ዘኁ 32:34
ኤር. 48:22ዘኁ 32:3, 4
ኤር. 48:23ዘኁ 32:37፤ ኤር 48:1
ኤር. 48:23ዘኁ 32:37, 38፤ ኢያሱ 13:15, 17፤ ሕዝ 25:9
ኤር. 48:24አሞጽ 2:2
ኤር. 48:26ኤር 48:42
ኤር. 48:26ኤር 25:15, 16
ኤር. 48:27ሰቆ 2:15፤ ሶፎ 2:8
ኤር. 48:29ኢሳ 16:6፤ 25:10, 11፤ ሶፎ 2:9, 10
ኤር. 48:312ነገ 3:24, 25፤ ኢሳ 16:7
ኤር. 48:32ዘኁ 32:37, 38፤ ኢያሱ 13:15, 19
ኤር. 48:32ዘኁ 21:32፤ 32:34, 35፤ ኢያሱ 21:8, 39
ኤር. 48:32ኢሳ 16:8, 9፤ ኤር 48:8
ኤር. 48:33ኤር 25:10
ኤር. 48:33ኢሳ 16:10
ኤር. 48:34ዘኁ 21:25፤ ኢያሱ 13:15, 17
ኤር. 48:34ዘኁ 32:37፤ ኢሳ 16:9
ኤር. 48:34ዘኁ 21:23
ኤር. 48:34ኤር 48:2, 3
ኤር. 48:34ኢሳ 15:4-6
ኤር. 48:36ኢሳ 16:11
ኤር. 48:37ኤር 16:6
ኤር. 48:37ዘሌ 19:28
ኤር. 48:37ዘፍ 37:34፤ ኢሳ 15:2, 3
ኤር. 48:40ሰቆ 4:19፤ ዕን 1:8
ኤር. 48:40ኤር 49:22
ኤር. 48:42ኤር 30:11
ኤር. 48:42ኤር 48:29
ኤር. 48:45ዘኁ 21:26, 28
ኤር. 48:45ዘኁ 24:17፤ አሞጽ 2:2
ኤር. 48:46ዘኁ 21:29፤ 1ነገ 11:7
ኤር. 48:46ኤር 48:7
ኤር. 48:47ሕዝ 25:11
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
  • 32
  • 33
  • 34
  • 35
  • 36
  • 37
  • 38
  • 39
  • 40
  • 41
  • 42
  • 43
  • 44
  • 45
  • 46
  • 47
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኤርምያስ 48:1-47

ኤርምያስ

48 የእስራኤል አምላክ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ስለ ሞዓብ+ እንዲህ ይላል፦

“ወዮ፣ ነቦ+ ጠፍታለችና!

ቂርያታይም+ ኀፍረት ተከናንባለች፤ ደግሞም ተይዛለች።

አስተማማኝ የሆነው መጠጊያ ተዋርዷል፤ ፈራርሷልም።+

 2 ከእንግዲህ ሞዓብን አያወድሷትም።

ለውድቀት ትዳረግ ዘንድ፣

‘ኑ ብሔር መሆኗ እንዲያከትም እንደምስሳት’ ብለው በሃሽቦን+ ይዶልቱባታል።

አንቺም ማድመን ሆይ፣ ዝም በይ፤

ከኋላሽ ሰይፍ ይከተልሻልና።

 3 ከሆሮናይም+ የጩኸት ድምፅ

እንዲሁም የጥፋትና የታላቅ ውድቀት ድምፅ ይሰማል።

 4 ሞዓብ ጠፍታለች።

ልጆቿ ይጮኻሉ።

 5 ወደ ሉሂት በሚወስደው አቀበት እያለቀሱ ይወጣሉ።

በደረሰው ጥፋት የተነሳ፣ ከሆሮናይም ቁልቁል በሚወስደው መንገድ ሲወርዱም የጭንቅ ጩኸት ይሰማሉ።+

 6 ሽሹ፤ ሕይወታችሁን አትርፉ!*

በምድረ በዳ እንዳለ የጥድ ዛፍ ሁኑ።

 7 ምክንያቱም አንቺ በሥራሽና ውድ በሆነ ሀብትሽ ትታመኛለሽ፤

ደግሞም ትያዣለሽ።

ከሞሽ+ ከካህናቱና ከመኳንንቱ ጋር

በአንድነት በግዞት ይወሰዳል።

 8 አጥፊው በእያንዳንዱ ከተማ ላይ ይመጣል፤

አንድም ከተማ አያመልጥም።+

ይሖዋ በተናገረው መሠረት

ሸለቆው* ይጠፋል፤ ደልዳላውም መሬት* እንዳልነበረ ይሆናል።

 9 ለሞዓብ ምልክት አቁሙ፤

ስትፈራርስ ትሸሻለችና፤

ከተሞቿም አስፈሪ ቦታ ይሆናሉ፤

የሚቀመጥባቸውም ሰው አይኖርም።+

10 ይሖዋ የሰጠውን ተልእኮ በግድየለሽነት የሚያከናውን የተረገመ ነው!

ሰይፉን ደም ከማፍሰስ የሚመልስ ሰው የተረገመ ነው!

11 ሞዓባውያን ከልጅነታቸው ጀምሮ

በአምቡላው ላይ እንደረጋ ወይን ጠጅ ተረጋግተው ተቀምጠዋል።

ከአንዱ ዕቃ ወደ ሌላው ዕቃ አልተገላበጡም፤

በግዞትም ተወስደው አያውቁም።

በዚህም ምክንያት ቃናቸው እንዳለ ነው፤

መዓዛቸውም አልተለወጠም።

12 “‘ስለዚህ፣ እነሆ እነሱን እንዲገለብጡ ሰዎችን የምልክበት ጊዜ ይመጣል’ ይላል ይሖዋ። ‘እነሱም ይገለብጧቸዋል፤ ዕቃዎቻቸውንም ባዶ ያስቀራሉ፤ ትላልቅ እንስራዎቻቸውንም ይሰባብራሉ። 13 የእስራኤል ቤት ይተማመንበት በነበረው በቤቴል እንዳፈረ ሁሉ ሞዓባውያንም በከሞሽ ያፍራሉ።+

14 “እኛ ለውጊያ የተዘጋጀን ኃያላን ተዋጊዎች ነን” በማለት እንዴት በድፍረት ትናገራላችሁ?’+

15 የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ተብሎ የሚጠራው ንጉሥ+ እንዲህ ይላል፦

‘ሞዓብ ጠፍታለች፤

ከተሞቿ ተወረዋል፤+

ምርጥ የሆኑት ወጣቶቻቸውም ታርደዋል።’+

16 በሞዓባውያን ላይ የሚደርሰው ጥፋት ቀርቧል፤

ውድቀታቸውም በፍጥነት እየቀረበ ነው።+

17 በዙሪያቸው ያሉ ሁሉ፣

ስማቸውን የሚያውቁ ሁሉ አብረዋቸው ያዝናሉ።

‘ኃያሉ በትር፣ የውበትም ዘንግ እንዴት ተሰበረ!’ በሏቸው።

18 አንቺ በዲቦን+ የምትኖሪ ሴት ልጅ ሆይ፣

ከክብርሽ ውረጂ፤ ተጠምተሽም* ተቀመጪ፤

የሞዓብ አጥፊ በአንቺ ላይ መጥቶብሻልና፤

የተመሸጉ ቦታዎችሽንም ያፈራርሳል።+

19 አንቺ በአሮዔር+ የምትኖሪ፣ መንገዱ አጠገብ ቆመሽ ተመልከቺ።

የሚሸሸውን ወንድና የምታመልጠውን ሴት ‘ምን ተፈጠረ?’ ብለሽ ጠይቂ።

20 ሞዓብ ኀፍረት ተከናነበች፤ በሽብርም ተውጣለች።

ዋይ ዋይ በሉ፤ እንዲሁም ጩኹ።

ሞዓብ መጥፋቷን በአርኖን+ አውጁ።

21 “ፍርድ ወደ ደልዳላው መሬት* መጥቷል፤+ በሆሎን፣ በያሃጽና+ በመፋአት፣+ 22 በዲቦን፣+ በነቦና+ በቤትዲብላታይም፣ 23 በቂርያታይም፣+ በቤትጋሙልና በቤትምዖን፣+ 24 በቀሪዮትና+ በቦስራ እንዲሁም በሩቅና በቅርብ ባሉ የሞዓብ ከተሞች ሁሉ ላይ መጥቷል።

25 ‘የሞዓብ ብርታት* ተቆርጧል፤

ክንዱም ተሰብሯል’ ይላል ይሖዋ።

26 ‘በይሖዋ ላይ ስለ ታበየ+ አስክሩት።+

ሞዓብ በትፋቱ ላይ ይንከባለላል፤

መሳለቂያም ሆኗል።

27 እስራኤል የአንተ መሳለቂያ ሆኖ አልነበረም?+

ራስህን የምትነቀንቀውና እሱን የምትቃወመው

እስራኤል ከሌቦች ጋር ተገኝቶ ነው?

28 እናንተ የሞዓብ ነዋሪዎች፣ ከከተሞቹ ወጥታችሁ በቋጥኝ ላይ ኑሩ፤

በገደል አፋፍ ጎጆዋን እንደምትሠራ ርግብም ሁኑ።’”

29 “ስለ ሞዓብ ኩራት ሰምተናል፤ እሱ በጣም ትዕቢተኛ ነው፤

ስለ እብሪቱ፣ ስለ ኩራቱ፣ ስለ ትዕቢቱና ስለ ልቡ ማበጥ ሰምተናል።”+

30 “‘ቁጣውን አውቃለሁ’ ይላል ይሖዋ፤

‘ሆኖም ጉራው ከንቱ ይሆናል።

አንዳች ነገር አያደርጉም።

31 ከዚህ የተነሳ ለሞዓብ አለቅሳለሁ፤

ለሞዓብ ምድር ሁሉ እጮኻለሁ፤

ለቂርሄረስ+ ነዋሪዎችም እቃትታለሁ።

32 የሲብማ+ ወይን ሆይ፣ ለያዜር+ ከተለቀሰው በበለጠ

ለአንቺ አለቅሳለሁ።

የተንዠረገጉት ቅርንጫፎችሽ ባሕሩን ተሻግረዋል።

እስከ ባሕሩ፣ እስከ ያዜርም ደርሰዋል።

አጥፊው በበጋ ፍሬሽና*

ለመከር በደረሰው ወይንሽ ላይ መጥቷል።+

33 ከፍራፍሬ እርሻውና ከሞዓብ ምድር

ሐሴትና ደስታ ጠፍቷል።+

ከወይን መጭመቂያዎቹ የወይን ጠጅ መፍሰሱን እንዲያቆም አድርጌአለሁ።

በእልልታ ወይን የሚረግጥ ሰው አይኖርም።

ጩኸቱ ለየት ያለ ጩኸት ይሆናል።’”+

34 “‘በሃሽቦን+ የሚያስተጋባው ጩኸት እስከ ኤልዓሌ+ ድረስ ይሰማል።

እስከ ያሃጽ+ ድረስ ድምፃቸውን ያሰማሉ፤

በዞአር የሚያስተጋባው ጩኸት እስከ ሆሮናይምና+ እስከ ኤግላት ሸሊሺያ ድረስ ይሰማል።

የኒምሪም ውኃዎች እንኳ ይደርቃሉ።+

35 ከፍ ባለ የማምለኪያ ቦታ ላይ መባ የሚያቀርበውንና

ለአምላኩ መሥዋዕት የሚያቀርበውን ሰው

ከሞዓብ አጠፋለሁ’ ይላል ይሖዋ።

36 ‘ስለዚህ ልቤ ለሞዓብ እንደ ዋሽንት* በሐዘን ያንጎራጉራል፤*+

ለቂርሄረስ ሰዎችም ልቤ እንደ ዋሽንት* በሐዘን ያንጎራጉራል።*

ያከማቸው ሀብት ይጠፋልና።

37 ራስ ሁሉ ተመልጧል፤+

ጢምም ሁሉ ተላጭቷል።

እጅ ሁሉ ተሸንትሯል፤+

በወገባቸውም ላይ ማቅ ታጥቀዋል!’”+

38 “‘በሞዓብ ጣሪያዎች ሁሉና

በአደባባዮቿ ሁሉ ላይ

ከዋይታ ሌላ የሚሰማ ነገር የለም።

ሞዓብን እንደተጣለ እንስራ

ሰባብሬአታለሁና’ ይላል ይሖዋ።

39 ‘እጅግ ተሸብራለች! ዋይ ዋይ በሉ!

ሞዓብ ኀፍረት ተከናንቦ ጀርባውን አዙሯል!

ሞዓብ መሳለቂያ ሆኗል፤

በዙሪያው ያሉት ሁሉ ከእሱ የተነሳ ይደነግጣሉ።’”

40 “ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦

‘እነሆ፣ ተወንጭፎ እንደሚወርድ ንስር፣+

እሱም በሞዓብ ላይ ክንፎቹን ይዘረጋል።+

41 ከተሞቹ ይወረራሉ፤

ምሽጎቿም ይያዛሉ።

በዚያ ቀን የሞዓብ ተዋጊዎች ልብ

ምጥ እንደያዛት ሴት ልብ ይሆናል።’”

42 “‘ሞዓብም ሕዝብ መሆኑ ያከትማል፤+

በይሖዋ ላይ ታብዮአልና።+

43 የሞዓብ ነዋሪ ሆይ፣

ሽብር፣ ጉድጓድና ወጥመድ ይጠብቅሃል’ ይላል ይሖዋ።

44 ‘ከሽብር የሚሸሽ ሁሉ ጉድጓዱ ውስጥ ይወድቃል፤

ከጉድጓዱም የሚወጣ ሁሉ በወጥመዱ ይያዛል።’

‘የሚቀጡበትን ዓመት በሞዓብ ላይ አመጣለሁና’ ይላል ይሖዋ።

45 ‘የሚሸሹት ሰዎች ኃይላቸው ተሟጦ በሃሽቦን ጥላ ሥር ይቆማሉ።

ከሃሽቦን እሳት፣

ከሲሖን መካከልም ነበልባል ይወጣልና።+

የሞዓብን ግንባርና

የሁከት ልጆችን ራስ ቅል ይበላል።’+

46 ‘ሞዓብ ሆይ፣ ወዮልህ!

የከሞሽ+ ሰዎች ጠፍተዋል።

ወንዶች ልጆችህ ተማርከዋልና፤

ሴቶች ልጆችህም በግዞት ተወስደዋል።+

47 በዘመኑ መጨረሻ ግን፣ ከሞዓብ የተማረኩትን እሰበስባለሁ’ ይላል ይሖዋ።

‘በሞዓብ ላይ የተላለፈው የፍርድ መልእክት እዚህ ላይ ይደመደማል።’”+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ