የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 1 ሳሙኤል 28
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

1 ሳሙኤል የመጽሐፉ ይዘት

      • ሳኦል በኤንዶር የምትኖር አንዲት መናፍስት ጠሪ ጠየቀ  (1-25)

1 ሳሙኤል 28:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 14:52
  • +1ሳሙ 27:12፤ 29:3

1 ሳሙኤል 28:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “በዘመኑ ሁሉ የራሴ ጠባቂ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 29:2

1 ሳሙኤል 28:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 25:1
  • +ዘፀ 22:18፤ ዘሌ 19:31፤ 20:6, 27፤ ዘዳ 18:10, 11፤ ራእይ 21:8

1 ሳሙኤል 28:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 19:17, 18፤ 2ነገ 4:8
  • +1ሳሙ 31:1፤ 2ሳሙ 1:21፤ 21:12

1 ሳሙኤል 28:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 28:20

1 ሳሙኤል 28:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 14:37
  • +ዘፀ 28:30፤ ዘኁ 27:21

1 ሳሙኤል 28:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 22:18፤ ዘሌ 19:31፤ 20:6፤ 1ሳሙ 15:23፤ 28:3
  • +ኢያሱ 17:11

1 ሳሙኤል 28:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 18:10, 11፤ 1ዜና 10:13

1 ሳሙኤል 28:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴን ልታጠምድ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 28:3
  • +ዘፀ 22:18፤ ዘሌ 20:27

1 ሳሙኤል 28:12

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ሳሙኤልን መስሎ የቀረበውን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 28:3

1 ሳሙኤል 28:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 15:27

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    1/1/2010፣ ገጽ 20

    ማመራመር፣ ገጽ 383-384

1 ሳሙኤል 28:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 28:6
  • +ዘሌ 19:31

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    ለዘላለም መኖር፣ ገጽ 91-92

1 ሳሙኤል 28:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 15:23፤ 16:14

1 ሳሙኤል 28:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 13:14፤ 15:28፤ 16:13፤ 24:20

1 ሳሙኤል 28:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 15:9፤ 1ዜና 10:13

1 ሳሙኤል 28:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 28:1፤ 31:1
  • +1ሳሙ 31:5
  • +1ሳሙ 31:2፤ 2ሳሙ 2:8
  • +1ሳሙ 31:7

1 ሳሙኤል 28:21

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴን በእጄ ይዤም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 20:27

1 ሳሙኤል 28:24

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ሠዋችው።”

1 ሳሙኤል 28:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 28:8

ተዛማጅ ሐሳብ

1 ሳሙ. 28:11ሳሙ 14:52
1 ሳሙ. 28:11ሳሙ 27:12፤ 29:3
1 ሳሙ. 28:21ሳሙ 29:2
1 ሳሙ. 28:31ሳሙ 25:1
1 ሳሙ. 28:3ዘፀ 22:18፤ ዘሌ 19:31፤ 20:6, 27፤ ዘዳ 18:10, 11፤ ራእይ 21:8
1 ሳሙ. 28:4ኢያሱ 19:17, 18፤ 2ነገ 4:8
1 ሳሙ. 28:41ሳሙ 31:1፤ 2ሳሙ 1:21፤ 21:12
1 ሳሙ. 28:51ሳሙ 28:20
1 ሳሙ. 28:61ሳሙ 14:37
1 ሳሙ. 28:6ዘፀ 28:30፤ ዘኁ 27:21
1 ሳሙ. 28:7ዘፀ 22:18፤ ዘሌ 19:31፤ 20:6፤ 1ሳሙ 15:23፤ 28:3
1 ሳሙ. 28:7ኢያሱ 17:11
1 ሳሙ. 28:8ዘዳ 18:10, 11፤ 1ዜና 10:13
1 ሳሙ. 28:91ሳሙ 28:3
1 ሳሙ. 28:9ዘፀ 22:18፤ ዘሌ 20:27
1 ሳሙ. 28:121ሳሙ 28:3
1 ሳሙ. 28:141ሳሙ 15:27
1 ሳሙ. 28:151ሳሙ 28:6
1 ሳሙ. 28:15ዘሌ 19:31
1 ሳሙ. 28:161ሳሙ 15:23፤ 16:14
1 ሳሙ. 28:171ሳሙ 13:14፤ 15:28፤ 16:13፤ 24:20
1 ሳሙ. 28:181ሳሙ 15:9፤ 1ዜና 10:13
1 ሳሙ. 28:191ሳሙ 28:1፤ 31:1
1 ሳሙ. 28:191ሳሙ 31:5
1 ሳሙ. 28:191ሳሙ 31:2፤ 2ሳሙ 2:8
1 ሳሙ. 28:191ሳሙ 31:7
1 ሳሙ. 28:21ዘሌ 20:27
1 ሳሙ. 28:251ሳሙ 28:8
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
1 ሳሙኤል 28:1-25

አንደኛ ሳሙኤል

28 በዚያም ዘመን ፍልስጤማውያን ከእስራኤል ጋር ለመዋጋት ሠራዊታቸውን አሰባሰቡ።+ በመሆኑም አንኩስ ዳዊትን “መቼም አንተና ሰዎችህ አብራችሁኝ ወደ ጦርነት እንደምትወጡ ታውቃለህ” አለው።+ 2 ዳዊትም አንኩስን “አገልጋይህ ምን እንደሚያደርግ አንተ በእርግጥ ታውቃለህ” አለው። ከዚያም አንኩስ ዳዊትን “እኔም በቋሚነት የግል ጠባቂዬ* እንድትሆን የምሾምህ ለዚህ ነው” አለው።+

3 በዚህ ጊዜ ሳሙኤል ሞቶ ነበር፤ እስራኤላውያንም ሁሉ አልቅሰውለት በገዛ ከተማው በራማ+ ቀብረውት ነበር። ሳኦልም መናፍስት ጠሪዎችንና ጠንቋዮችን ከምድሪቱ አስወግዶ ነበር።+

4 ፍልስጤማውያንም ተሰብስበው በመምጣት በሹነም+ ሰፈሩ። ሳኦል ደግሞ እስራኤላውያንን በሙሉ አሰባሰበ፤ እነሱም በጊልቦአ+ ሰፈሩ። 5 ሳኦል የፍልስጤማውያንን ሠራዊት ባየ ጊዜ ፈራ፤ ልቡም እጅግ ተሸበረ።+ 6 ሳኦል ይሖዋን ቢጠይቅም+ ይሖዋ በሕልምም ሆነ በኡሪም+ አሊያም በነቢያት በኩል መልስ አልሰጠውም። 7 በመጨረሻም ሳኦል አገልጋዮቹን “መናፍስት ጠሪ+ ፈልጉልኝ፤ እኔም ሄጄ ምክር እጠይቃታለሁ” አላቸው። አገልጋዮቹም “በኤንዶር+ አንዲት መናፍስት ጠሪ አለች” በማለት መለሱለት።

8 በመሆኑም ሳኦል ማንነቱን ሰውሮና ሌላ ልብስ ለብሶ ከሁለት ሰዎች ጋር በመሆን በሌሊት ወደ ሴትየዋ ሄደ። እሱም “እባክሽ፣ መናፍስትን ጠርተሽ+ ጠንቁይልኝ፤ የምነግርሽንም ሰው አስነሺልኝ” አላት። 9 ሆኖም ሴትየዋ እንዲህ አለችው፦ “ሳኦል መናፍስት ጠሪዎችንና ጠንቋዮችን ከምድሪቱ በማስወገድ ምን እንዳደረገ አንተ ራስህ በሚገባ ታውቃለህ።+ ታዲያ እኔ እንድገደል ልታጠምደኝ* የምትሞክረው ለምንድን ነው?”+ 10 ከዚያም ሳኦል “ሕያው በሆነው በይሖዋ እምላለሁ፣ በዚህ ጉዳይ በጥፋተኝነት አትጠየቂም!” በማለት በይሖዋ ማለላት። 11 በዚህ ጊዜ ሴትየዋ “እሺ ማንን ላስነሳልህ?” አለችው። እሱም “ሳሙኤልን አስነሺልኝ” አላት። 12 ሴትየዋም “ሳሙኤልን”*+ ስታየው በኃይል ጮኸች፤ ከዚያም ሳኦልን “ያታለልከኝ ለምንድን ነው? አንተ ሳኦል አይደለህ!” አለችው። 13 ንጉሡም “አትፍሪ፤ ለመሆኑ ምን እያየሽ ነው?” አላት። ሴትየዋም ለሳኦል “አማልክትን የሚመስል ከምድር ሲወጣ አያለሁ” ስትል መለሰችለት። 14 እሱም ወዲያውኑ “ምን ይመስላል?” አላት፤ እሷም “የወጣው አንድ አረጋዊ ሰው ነው፤ እጅጌ የሌለው ቀሚስ ለብሷል”+ አለችው። በዚህ ጊዜ ሳኦል የወጣው “ሳሙኤል” እንደሆነ ተገነዘበ፤ በግንባሩም መሬት ላይ ተደፍቶ ሰገደ።

15 ከዚያም “ሳሙኤል” ሳኦልን “እንድነሳ በማድረግ ለምን ትረብሸኛለህ?” አለው። ሳኦልም እንዲህ አለው፦ “ከባድ ጭንቅ ውስጥ ገብቻለሁ። ፍልስጤማውያን እየወጉኝ ነው፤ አምላክም ከእኔ ርቋል፤ በነቢያትም ሆነ በሕልም አማካኝነት መልስ አይሰጠኝም፤+ ስለሆነም ምን ማድረግ እንዳለብኝ እንድትነግረኝ ጠራሁህ።”+

16 “ሳሙኤልም” እንዲህ አለው፦ “ታዲያ ይሖዋ ከራቀህና+ ጠላት ከሆነብህ እኔን ለምን ትጠይቀኛለህ? 17 ይሖዋ በእኔ በኩል አስቀድሞ የተናገረውን ይፈጽማል፦ ይሖዋ መንግሥትን ከእጅህ ነጥቆ ከባልንጀሮችህ አንዱ ለሆነው ለዳዊት ይሰጠዋል።+ 18 የይሖዋን ቃል ስላልሰማህና በአማሌቃውያን ላይ የነደደውን ቁጣውን ስላላስፈጸምክ+ ይሖዋ በዚህ ቀን ይህን ያደርግብሃል። 19 ይሖዋ አንተንም ሆነ እስራኤላውያንን ለፍልስጤማውያን+ አሳልፎ ይሰጣችኋል፤ ነገ አንተና+ ልጆችህ+ ከእኔ ጋር ትሆናላችሁ። በተጨማሪም ይሖዋ የእስራኤልን ሠራዊት ለፍልስጤማውያን አሳልፎ ይሰጣል።”+

20 በዚህ ጊዜ ሳኦል በቁመቱ መሬት ላይ ተዘረረ፤ “ሳሙኤል” በተናገረውም ቃል የተነሳ በከፍተኛ ፍርሃት ተዋጠ። ደግሞም ሙሉ ቀንና ሙሉ ሌሊት እህል ስላልቀመሰ አቅሙ ተሟጠጠ። 21 ሴትየዋም ወደ ሳኦል መጥታ በጣም እንደተረበሸ ስታይ እንዲህ አለችው፦ “እንግዲህ እኔ አገልጋይህ ቃልህን ሰምቻለሁ፤ ሕይወቴን አደጋ ላይ ጥዬም*+ እንዳደርገው የነገርከኝን ፈጽሜአለሁ። 22 አሁንም እባክህ፣ የአገልጋይህን ቃል ስማ። ትንሽ ምግብ ላቅርብልህና ብላ፤ ከዚያም ለመሄድ የሚያስችል ብርታት ታገኛለህ።” 23 እሱ ግን “አልበላም” በማለት እንቢ አለ። ሆኖም አገልጋዮቹና ሴትየዋ አጥብቀው ለመኑት። በመጨረሻም ቃላቸውን በመስማት ከመሬት ተነስቶ አልጋ ላይ ተቀመጠ። 24 ሴትየዋም ቤት ውስጥ አንድ የሰባ ጥጃ ነበራት፤ ስለዚህ ፈጠን ብላ ጥጃውን አረደችው፤* ከዚያም ዱቄት ወስዳ ካቦካች በኋላ ቂጣ ጋገረች። 25 ለሳኦልና ለአገልጋዮቹም አቀረበችላቸው፤ እነሱም በሉ። ከዚያም ተነስተው በሌሊት ሄዱ።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ