የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፍጥረት 43
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘፍጥረት የመጽሐፉ ይዘት

      • የዮሴፍ ወንድሞች ቢንያምን ይዘው ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ግብፅ ሄዱ (1-14)

      • ዮሴፍ በድጋሚ ከወንድሞቹ ጋር ተገናኘ (15-23)

      • ዮሴፍ ከወንድሞቹ ጋር በማዕድ ተቀመጠ (24-34)

ዘፍጥረት 43:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 41:30፤ ሥራ 7:11

ዘፍጥረት 43:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:1, 2

ዘፍጥረት 43:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:15

ዘፍጥረት 43:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:15

ዘፍጥረት 43:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 32:28

ዘፍጥረት 43:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:13
  • +ዘፍ 42:16

ዘፍጥረት 43:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሥራ 7:14
  • +ዘፍ 42:1, 2
  • +ዘፍ 37:26፤ 42:38

ዘፍጥረት 43:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ለእሱ ዋስ እሆናለሁ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 44:32

ዘፍጥረት 43:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 8:22፤ ሕዝ 27:17
  • +ዘፍ 37:25
  • +ዘፍ 32:20

ዘፍጥረት 43:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:25, 35

ዘፍጥረት 43:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:36

ዘፍጥረት 43:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:7, 9

ዘፍጥረት 43:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 41:39, 40

ዘፍጥረት 43:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:25, 35

ዘፍጥረት 43:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:3

ዘፍጥረት 43:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:27

ዘፍጥረት 43:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 43:12

ዘፍጥረት 43:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:23, 24

ዘፍጥረት 43:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 43:16
  • +ዘፍ 43:11

ዘፍጥረት 43:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:7, 9፤ 42:6

ዘፍጥረት 43:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 43:7

ዘፍጥረት 43:28

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:7, 9

ዘፍጥረት 43:29

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 35:24
  • +ዘፍ 42:13

ዘፍጥረት 43:30

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:23, 24

ዘፍጥረት 43:32

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 46:33, 34፤ ዘፀ 8:26

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    1/15/2004፣ ገጽ 29

ዘፍጥረት 43:33

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “እነሱም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 49:3፤ ዘዳ 21:17

ዘፍጥረት 43:34

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 45:22

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘፍ. 43:1ዘፍ 41:30፤ ሥራ 7:11
ዘፍ. 43:2ዘፍ 42:1, 2
ዘፍ. 43:3ዘፍ 42:15
ዘፍ. 43:5ዘፍ 42:15
ዘፍ. 43:6ዘፍ 32:28
ዘፍ. 43:7ዘፍ 42:13
ዘፍ. 43:7ዘፍ 42:16
ዘፍ. 43:8ሥራ 7:14
ዘፍ. 43:8ዘፍ 42:1, 2
ዘፍ. 43:8ዘፍ 37:26፤ 42:38
ዘፍ. 43:9ዘፍ 44:32
ዘፍ. 43:11ኤር 8:22፤ ሕዝ 27:17
ዘፍ. 43:11ዘፍ 37:25
ዘፍ. 43:11ዘፍ 32:20
ዘፍ. 43:12ዘፍ 42:25, 35
ዘፍ. 43:14ዘፍ 42:36
ዘፍ. 43:15ዘፍ 37:7, 9
ዘፍ. 43:17ዘፍ 41:39, 40
ዘፍ. 43:18ዘፍ 42:25, 35
ዘፍ. 43:20ዘፍ 42:3
ዘፍ. 43:21ዘፍ 42:27
ዘፍ. 43:22ዘፍ 43:12
ዘፍ. 43:23ዘፍ 42:23, 24
ዘፍ. 43:25ዘፍ 43:16
ዘፍ. 43:25ዘፍ 43:11
ዘፍ. 43:26ዘፍ 37:7, 9፤ 42:6
ዘፍ. 43:27ዘፍ 43:7
ዘፍ. 43:28ዘፍ 37:7, 9
ዘፍ. 43:29ዘፍ 35:24
ዘፍ. 43:29ዘፍ 42:13
ዘፍ. 43:30ዘፍ 42:23, 24
ዘፍ. 43:32ዘፍ 46:33, 34፤ ዘፀ 8:26
ዘፍ. 43:33ዘፍ 49:3፤ ዘዳ 21:17
ዘፍ. 43:34ዘፍ 45:22
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
  • 32
  • 33
  • 34
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘፍጥረት 43:1-34

ዘፍጥረት

43 ረሃቡ በምድሪቱ ላይ በርትቶ ነበር።+ 2 ስለሆነም ከግብፅ ያመጡትን እህል በልተው ሲጨርሱ+ አባታቸው “ተመልሳችሁ ሂዱና ጥቂት እህል ግዙልን” አላቸው። 3 በዚህ ጊዜ ይሁዳ እንዲህ አለው፦ “ሰውየው ‘ወንድማችሁን ይዛችሁት ካልመጣችሁ በምንም ዓይነት ዳግመኛ ፊቴን አታዩም’ በማለት በግልጽ አስጠንቅቆናል።+ 4 ወንድማችንን ከእኛ ጋር የምትልከው ከሆነ ወደዚያ ወርደን እህል እንገዛልሃለን። 5 እሱን የማትልከው ከሆነ ግን ወደዚያ አንወርድም፤ ምክንያቱም ሰውየው ‘ወንድማችሁን ይዛችሁት ካልመጣችሁ በምንም ዓይነት ዳግመኛ ፊቴን አታዩም’ ብሎናል።”+ 6 እስራኤልም+ “ምነው እንዲህ ላለ ችግር ዳረጋችሁኝ? ሌላ ወንድም እንዳላችሁ ለምን ለሰውየው ነገራችሁት?” አላቸው። 7 እነሱም እንዲህ አሉት፦ “ሰውየው ‘አባታችሁ አሁንም በሕይወት አለ? ሌላስ ወንድም አላችሁ?’ በማለት በቀጥታ ስለ እኛና ስለ ዘመዶቻችን ጠየቀን፤ እኛም ለጥያቄው መልስ ሰጠነው።+ ታዲያ ‘ወንድማችሁን ይዛችሁ ኑ’ ይለናል ብለን እንዴት ልንጠረጥር እንችላለን?”+

8 ከዚያም ይሁዳ አባቱን እስራኤልን እንዲህ በማለት ለመነው፦ “እኛም ሆን አንተ እንዲሁም ትናንሽ ልጆቻችን+ በረሃብ ከምናልቅ፣ በሕይወት እንድንተርፍ+ ልጁ ከእኔ ጋር እንዲሄድ ፍቀድና+ ተነስተን ወደዚያ እንሂድ። 9 የልጁን ደህንነት በተመለከተ ኃላፊነቱን እኔ እወስዳለሁ።*+ አንድ ነገር ቢሆን እኔን ተጠያቂ ልታደርገኝ ትችላለህ። ልጁን ወደ አንተ መልሼ ባላመጣውና ባላስረክብህ በሕይወቴ ሙሉ በፊትህ በደለኛ ልሁን። 10 ዝም ብለን ጊዜ ባናጠፋ ኖሮ እስካሁን ሁለት ጊዜ እዚያ ደርሰን በተመለስን ነበር።”

11 በመሆኑም አባታቸው እስራኤል እንዲህ አላቸው፦ “እንግዲህ ሌላ አማራጭ ከጠፋ እንዲህ አድርጉ፦ ምድሪቱ ከምታፈራቸው ምርጥ ነገሮች መካከል ጥቂት በለሳን፣+ ጥቂት ማር፣ ጥሩ መዓዛ ያለው ሙጫ፣ ከርቤ፣+ ለውዝና አልሞንድ ለሰውየው ስጦታ+ እንዲሆን በከረጢቶቻችሁ ይዛችሁ ውረዱ። 12 በተጨማሪም እጥፍ ገንዘብ ያዙ፤ በከረጢቶቻችሁ አፍ ላይ ተደርጎ የተመለሰላችሁንም ገንዘብ ይዛችሁ ሂዱ።+ ምናልባት በስህተት የመጣ ሊሆን ይችላል። 13 በሉ ተነሱና ወንድማችሁን ይዛችሁ ወደ ሰውየው ሂዱ። 14 ሌላውን ወንድማችሁንና ቢንያምን እንዲለቅላችሁ ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ የሰውየውን ልብ ያራራላችሁ። እንግዲህ ልጆቼን አጥቼ ለሐዘን ከተዳረግኩም ምን አደርጋለሁ፤ የመጣውን እቀበላለሁ!”+

15 ስለዚህ ሰዎቹ ይህን ስጦታና እጥፍ ገንዘብ እንዲሁም ቢንያምን ይዘው ተነሱ። ወደ ግብፅም ወረዱ፤ እንደገናም ዮሴፍ ፊት ቀረቡ።+ 16 ዮሴፍ ቢንያምን ከእነሱ ጋር ሲያየው የቤቱ ኃላፊ የሆነውን ሰው ወዲያውኑ እንዲህ አለው፦ “ሰዎቹን ወደ ቤት ውሰዳቸው፤ አብረውኝ ምሳ ስለሚበሉ እንስሳ አርደህ ምግብ አዘጋጅ።” 17 ሰውየውም ወዲያውኑ ልክ ዮሴፍ እንዳለው አደረገ፤+ ሰዎቹንም ወደ ዮሴፍ ቤት ወሰዳቸው። 18 ሰዎቹ ግን ወደ ዮሴፍ ቤት ሲወሰዱ ፈሩ፤ እንዲህም ይሉ ጀመር፦ “ወደዚህ ያመጡን ባለፈው ጊዜ በከረጢቶቻችን ውስጥ በተመለሰው ገንዘብ የተነሳ ነው። በቃ አሁን ያሠቃዩናል፤ ባሪያ ያደርጉናል፤ አህዮቻችንንም ይቀሙናል!”+

19 በመሆኑም የዮሴፍ ቤት ኃላፊ ወደሆነው ሰው ቀርበው በቤቱ በራፍ ላይ አነጋገሩት። 20 እነሱም እንዲህ አሉት፦ “ይቅርታ ጌታዬ! እኛ ባለፈው ጊዜ ወደዚህ የመጣነው እህል ለመግዛት ነበር።+ 21 ሆኖም የምናርፍበት ቦታ ደርሰን ከረጢቶቻችንን ስንከፍት የእያንዳንዳችንን ገንዘብ ምንም ሳይጎድል በየከረጢታችን አፍ ላይ አገኘነው።+ ስለዚህ ራሳችን ገንዘቡን መመለስ እንፈልጋለን። 22 እህል ለመግዛት ተጨማሪ ገንዘብ ይዘናል። ገንዘባችንን በከረጢታችን ውስጥ መልሶ ያስቀመጠው ማን እንደሆነ አናውቅም።”+ 23 እሱም “አይዟችሁ፣ አትፍሩ። ይህን ገንዘብ በከረጢቶቻችሁ ውስጥ ያስቀመጠላችሁ የእናንተ አምላክና የአባታችሁ አምላክ ነው። እኔ እንደሆነ ገንዘባችሁ ደርሶኛል” አላቸው። ከዚያም ስምዖንን አውጥቶ ወደ እነሱ አመጣው።+

24 ከዚያም ሰውየው ሰዎቹን ወደ ዮሴፍ ቤት አስገባቸው፤ እግራቸውን እንዲታጠቡም ውኃ አቀረበላቸው፤ እንዲሁም ለአህዮቻቸው ገፈራ ሰጣቸው። 25 እነሱም እዚያው ምሳ እንደሚበሉ+ ስለሰሙ ዮሴፍ ቀትር ላይ ሲመጣ የሚሰጡትን ስጦታ+ ማዘገጃጀት ጀመሩ። 26 ዮሴፍ ወደ ቤት ሲገባ፣ ያዘጋጁትን ስጦታ ይዘው ወደ እሱ በመግባት አበረከቱለት፤ መሬት ላይም ተደፍተው ሰገዱለት።+ 27 ከዚያም ስለ ደህንነታቸው ጠየቃቸው፤ እንዲህም አላቸው፦ “ባለፈው ጊዜ የነገራችሁኝ አረጋዊ አባታችሁ ደህና ነው? አሁንም በሕይወት አለ?”+ 28 እነሱም “አገልጋይህ አባታችን ደህና ነው። አሁንም በሕይወት አለ” አሉት። ከዚያም መሬት ላይ ተደፍተው ሰገዱ።+

29 ዮሴፍም ቀና ብሎ ሲመለከት የእናቱን ልጅ ወንድሙን+ ቢንያምን አየ፤ እሱም “ባለፈው ጊዜ ስለ እሱ የነገራችሁኝ ትንሹ ወንድማችሁ ይሄ ነው?” አላቸው።+ ቢንያምንም “የእኔ ልጅ፣ አምላክ ሞገሱን ያሳይህ” አለው። 30 ዮሴፍ ወንድሙን ሲያይ ስሜቱን መቆጣጠር ስላቃተው በፍጥነት ወጣ፤ የሚያለቅስበትንም ቦታ ፈለገ። ብቻውን ወደ አንድ ክፍል ገብቶም አለቀሰ።+ 31 ከዚያም ፊቱን ተጣጥቦ ወጣ፤ እንደ ምንም ስሜቱን ተቆጣጥሮም “ምግብ ይቅረብ” አለ። 32 እነሱም ለዮሴፍ ለብቻው አቀረቡለት፤ ለእነሱም ለብቻቸው አቀረቡላቸው። እንዲሁም በቤቱ ለሚበሉት ግብፃውያን ለብቻቸው አቀረቡላቸው። ይህን ያደረጉት ግብፃውያን ከዕብራውያን ጋር አብረው ምግብ ስለማይበሉ ነው፤ ምክንያቱም ይህ ለግብፃውያን አስጸያፊ ነገር ነው።+

33 ወንድማማቾቹም* የበኩሩ እንደ ብኩርና መብቱ፣+ ታናሹም እንደ ታናሽነቱ በፊቱ ተቀመጡ፤ እርስ በርሳቸውም በመገረም ይተያዩ ነበር። 34 እሱም ፊቱ ከቀረበው ምግብ እየተነሳ ለእነሱ እንዲሰጣቸው ያደርግ ነበር፤ የቢንያም ድርሻ ግን ከሌሎቹ አምስት እጥፍ እንዲበልጥ ያደርግ ነበር።+ እነሱም እስኪጠግቡ ድረስ አብረውት በሉ፣ ጠጡም።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ