የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኤርምያስ 12
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኤርምያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • ኤርምያስ አቤቱታ አቀረበ (1-4)

      • ይሖዋ የሰጠው መልስ (5-17)

ኤርምያስ 12:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 18:25
  • +ኢዮብ 12:6፤ 21:7፤ መዝ 73:3፤ ኤር 5:28

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የስብሰባው አስተዋጽኦ የማመሣከሪያ ጽሑፎች፣ 3/2017፣ ገጽ 3

ኤርምያስ 12:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ጥልቅ ስሜታቸው።” ቃል በቃል “ኩላሊታቸው።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 29:13

ኤርምያስ 12:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 139:1, 2
  • +2ነገ 20:3፤ መዝ 17:3፤ ኤር 11:20

ኤርምያስ 12:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 14:6፤ 23:10

ኤርምያስ 12:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 4:13

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    2/1/2012፣ ገጽ 29

    3/15/2011፣ ገጽ 32

ኤርምያስ 12:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 9:4

ኤርምያስ 12:7

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴ እጅግ የምትወዳትን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሉቃስ 13:35
  • +ዘፀ 19:5፤ ኢሳ 47:6
  • +ሰቆ 2:1

ኤርምያስ 12:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እንደ ዥጉርጉር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 24:2፤ ሕዝ 16:37
  • +ኢሳ 56:9፤ ኤር 7:33

ኤርምያስ 12:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 80:8፤ ኢሳ 5:1, 7፤ ኤር 6:3
  • +ኢሳ 63:18፤ ኤር 3:19

ኤርምያስ 12:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “ያለቅሳል” ማለትም ሊሆን ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 9:11፤ 10:22
  • +ኢሳ 42:24, 25

ኤርምያስ 12:12

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ሥጋ ሁሉ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 26:33፤ ኤር 15:2

ኤርምያስ 12:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 26:16፤ ሚክ 6:15

ኤርምያስ 12:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 79:4፤ ኤር 48:26፤ ሕዝ 25:3፤ ዘካ 1:15፤ 2:8
  • +ኤር 48:2፤ 49:2

ኤርምያስ 12:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 60:12

ተዛማጅ ሐሳብ

ኤር. 12:1ዘፍ 18:25
ኤር. 12:1ኢዮብ 12:6፤ 21:7፤ መዝ 73:3፤ ኤር 5:28
ኤር. 12:2ኢሳ 29:13
ኤር. 12:3መዝ 139:1, 2
ኤር. 12:32ነገ 20:3፤ መዝ 17:3፤ ኤር 11:20
ኤር. 12:4ኤር 14:6፤ 23:10
ኤር. 12:5ኤር 4:13
ኤር. 12:6ኤር 9:4
ኤር. 12:7ሉቃስ 13:35
ኤር. 12:7ዘፀ 19:5፤ ኢሳ 47:6
ኤር. 12:7ሰቆ 2:1
ኤር. 12:92ነገ 24:2፤ ሕዝ 16:37
ኤር. 12:9ኢሳ 56:9፤ ኤር 7:33
ኤር. 12:10መዝ 80:8፤ ኢሳ 5:1, 7፤ ኤር 6:3
ኤር. 12:10ኢሳ 63:18፤ ኤር 3:19
ኤር. 12:11ኤር 9:11፤ 10:22
ኤር. 12:11ኢሳ 42:24, 25
ኤር. 12:12ዘሌ 26:33፤ ኤር 15:2
ኤር. 12:13ዘሌ 26:16፤ ሚክ 6:15
ኤር. 12:14መዝ 79:4፤ ኤር 48:26፤ ሕዝ 25:3፤ ዘካ 1:15፤ 2:8
ኤር. 12:14ኤር 48:2፤ 49:2
ኤር. 12:17ኢሳ 60:12
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኤርምያስ 12:1-17

ኤርምያስ

12 ይሖዋ ሆይ፣ አቤቱታዬን ለአንተ ሳቀርብ፣

ከፍትሕ ጋር ስለተያያዙ ጉዳዮች ሳናግርህ እነሆ፣ አንተ ጻድቅ ነህ።+

ታዲያ የክፉዎች መንገድ ለምን ይሰምራል?+

ደግሞስ ከዳተኞች ሳይጨነቁ የሚኖሩት ለምንድን ነው?

 2 አንተ ተክለሃቸዋል፤ እነሱም ሥር ሰደዋል።

አድገዋል፤ ፍሬም አፍርተዋል።

ከከንፈራቸው አይለዩህም፤ የውስጥ ሐሳባቸው* ግን ከአንተ የራቀ ነው።+

 3 ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ግን በሚገባ ታውቀኛለህ፤+ ታየኛለህም፤

ልቤን መረመርክ፤ ከአንተም ጋር የሚስማማ ሆኖ አገኘኸው።+

ለእርድ እንደተዘጋጁ በጎች ለያቸው፤

ለሚገደሉበትም ቀን ለይተህ አቆያቸው።

 4 ምድሪቱ ተራቁታ፣

የሜዳውም ተክል ሁሉ ደርቆ የሚቆየው እስከ መቼ ድረስ ነው?+

በምድሪቱ በሚኖሩት ሰዎች ክፋት የተነሳ

አራዊቱና ወፎቹ ተጠራርገው ጠፉ።

እነሱ፣ “ወደፊት ምን እንደሚገጥመን አያውቅም” ብለዋልና።

 5 ከእግረኞች ጋር ሮጠህ ከደከምክ፣

ከፈረሶች ጋር እንዴት ልትወዳደር ትችላለህ?+

በሰላም ምድር ተማምነህ ብትቀመጥ እንኳ

ጥቅጥቅ ባለው የዮርዳኖስ ጥሻ ውስጥ እንዴት ልትሆን ነው?

 6 የገዛ ወንድሞችህ፣

የገዛ አባትህ ቤተሰቦች እንኳ አታለውሃልና።+

እነሱ በአንተ ላይ ጮኸዋል።

መልካም ነገር ቢናገሩህ እንኳ

ፈጽሞ አትመናቸው።

 7 “ቤቴን ትቻለሁ፤+ ርስቴን ጥዬ ሄጃለሁ።+

እጅግ የምወዳትን* በጠላቶቿ እጅ አሳልፌ ሰጥቻታለሁ።+

 8 ርስቴ በጫካ ውስጥ እንዳለ አንበሳ ሆነችብኝ።

በእኔ ላይ ጮኻብኛለች።

በዚህም የተነሳ ጠላኋት።

 9 ርስቴ ለእኔ ብዙ ቀለማት እንዳለው* አዳኝ አሞራ ነች፤

ሌሎች አዳኝ አሞሮች ይከቧታል፤ ደግሞም ያጠቋታል።+

እናንተ የዱር አራዊት ሁሉ ኑ፤ በአንድነት ተሰብሰቡ፤

ትቀራመቷት ዘንድ ኑ።+

10 ብዙ እረኞች የወይን እርሻዬን አጥፍተውታል፤+

ይዞታዬንም ረግጠውታል።+

የተወደደውን ይዞታዬን ጠፍ ምድረ በዳ አድርገውታል።

11 ባድማ ሆኗል።

ደግሞም ተራቁቷል፤*

በፊቴ ወና ሆኗል።+

ምድሪቱ በሙሉ ባድማ ሆናለች፤

ይሁንና ይህን ልብ ያለ አንድም ሰው የለም።+

12 በምድረ በዳ ባሉት፣ በተበላሹ መንገዶች ሁሉ አጥፊዎች መጥተዋል፤

የይሖዋ ሰይፍ ከአንዱ ጫፍ እስከ ሌላኛው ጫፍ ድረስ ምድሪቱን ትበላለችና።+

ማንም ሰው* ሰላም የለውም።

13 ስንዴ ዘሩ፤ ሆኖም እሾህን አጨዱ።+

እስኪዝሉ ድረስ ሠሩ፤ ነገር ግን ምንም ጥቅም አላገኙም።

ከሚነደው የይሖዋ ቁጣ የተነሳ

በሚያገኙት ምርት ያፍራሉ።”

14 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “ሕዝቤ እስራኤል እንዲወርሰው ያደረግኩትን ርስት የሚነኩ ክፉ ጎረቤቶቼን ሁሉ+ ከምድራቸው እነቅላቸዋለሁ፤+ የይሁዳንም ቤት ከመካከላቸው እነቅላለሁ። 15 ከነቀልኳቸው በኋላ ግን ዳግመኛ ምሕረት አደርግላቸዋለሁ፤ እያንዳንዳቸውን ወደየርስታቸው፣ እያንዳንዳቸውንም ወደየምድራቸው እመልሳቸዋለሁ።”

16 “ሕዝቤን በባአል እንዲምሉ እንዳስተማሩ ሁሉ እነሱም የሕዝቤን መንገድ በእርግጥ ቢማሩና ‘ሕያው ይሖዋን!’ ብለው በስሜ ቢምሉ በሕዝቤ መካከል ጸንተው ይኖራሉ። 17 ይሁንና ከእነዚህ ብሔራት መካከል የማይታዘዝ ቢኖር ያን ብሔር እነቅለዋለሁ፤ ነቅዬም አጠፋዋለሁ” ይላል ይሖዋ።+

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ