የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኤርምያስ 4
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኤርምያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • ንስሐ መግባት በረከት ያስገኛል (1-4)

      • ከሰሜን ጥፋት ይመጣል (5-18)

      • ኤርምያስ የተሰማው ሐዘን (19-31)

ኤርምያስ 4:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 3:22፤ ኢዩ 2:12, 13

ኤርምያስ 4:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 65:16

ኤርምያስ 4:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሆሴዕ 10:12

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    3/15/2007፣ ገጽ 9

ኤርምያስ 4:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 9:25, 26
  • +ሰቆ 4:11

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    3/15/2013፣ ገጽ 9-10

    3/15/2007፣ ገጽ 9

ኤርምያስ 4:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 6:1
  • +ኤር 35:11

ኤርምያስ 4:6

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ለምልክት የሚተከል ምሰሶ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 1:14፤ 21:7፤ 25:9

ኤርምያስ 4:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 24:1፤ 25:1፤ ኤር 5:6፤ 50:17
  • +ሕዝ 26:7
  • +ኢሳ 5:9፤ 6:11፤ ኤር 2:15፤ 9:11

ኤርምያስ 4:8

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ደረታችሁን ምቱ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 6:26

ኤርምያስ 4:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “መኳንንቱ ወኔ ይከዳቸዋል።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 25:5
  • +ኢሳ 29:9, 10

ኤርምያስ 4:10

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ሰይፍ ነፍሳችን ላይ ደርሶ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 6:13, 14፤ 14:13፤ 23:16, 17
  • +ሕዝ 14:9

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    3/15/2007፣ ገጽ 9

ኤርምያስ 4:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    በሰውኛ ዘይቤ የተገለጸ ቅኔያዊ አነጋገር፤ አዘኔታን ወይም ርኅራኄን የሚያመለክት ሊሆን ይችላል።

  • *

    እህልን ወደ ላይ በመበተንና ለነፋስ በመስጠት ከገለባ መለየት።

ኤርምያስ 4:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 5:26, 28
  • +ዘዳ 28:49, 50፤ ሰቆ 4:19፤ ዕን 1:8

ኤርምያስ 4:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 1:16፤ ሕዝ 18:31

ኤርምያስ 4:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 8:16

ኤርምያስ 4:16

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ተመልካቾች።” መቼ ጥቃት መሰንዘር እንዳለባቸው ለመወሰን ከተማዋን የሚቃኙ ሰዎችን ያመለክታል።

ኤርምያስ 4:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 25:1, 2
  • +ኢሳ 63:10፤ ሕዝ 2:3

ኤርምያስ 4:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 107:17

ኤርምያስ 4:19

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “አንጀቴ።”

  • *

    “የውጊያ ሁካታ ድምፅ” ማለትም ሊሆን ይችላል።

  • *

    ወይም “ነፍሴ ሰምታለችና።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሶፎ 1:15, 16

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    11/1/1994፣ ገጽ 12

ኤርምያስ 4:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 10:20

ኤርምያስ 4:21

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ለምልክት የሚተከለውን ምሰሶ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 6:1

ኤርምያስ 4:22

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ጥበበኞች።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 32:6፤ ኤር 5:21

ኤርምያስ 4:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 9:10
  • +ኢሳ 5:30፤ ኢዩ 2:31

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    ማመራመር፣ ገጽ 365

ኤርምያስ 4:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 5:25

ኤርምያስ 4:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሶፎ 1:3

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    ማመራመር፣ ገጽ 365

ኤርምያስ 4:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 29:22, 23

ኤርምያስ 4:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 26:32፤ 2ዜና 36:20, 21፤ ኢሳ 6:11፤ ኤር 10:22፤ ሕዝ 33:28

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    ራእይ፣ ገጽ 109

    ማመራመር፣ ገጽ 365

ኤርምያስ 4:28

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “አልጸጸትም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 24:4፤ ኢዩ 1:10
  • +ኢሳ 5:30፤ ኢዩ 2:30, 31
  • +2ነገ 23:26፤ ሕዝ 24:14

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    ራእይ፣ ገጽ 109

ኤርምያስ 4:29

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 25:4
  • +ኢሳ 2:19

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    ማመራመር፣ ገጽ 365

ኤርምያስ 4:30

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍስሽን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 23:22, 26
  • +ሰቆ 1:2

ኤርምያስ 4:31

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴ ዝላለችና።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሰቆ 1:17

ተዛማጅ ሐሳብ

ኤር. 4:1ኤር 3:22፤ ኢዩ 2:12, 13
ኤር. 4:2ኢሳ 65:16
ኤር. 4:3ሆሴዕ 10:12
ኤር. 4:4ኤር 9:25, 26
ኤር. 4:4ሰቆ 4:11
ኤር. 4:5ኤር 6:1
ኤር. 4:5ኤር 35:11
ኤር. 4:6ኤር 1:14፤ 21:7፤ 25:9
ኤር. 4:72ነገ 24:1፤ 25:1፤ ኤር 5:6፤ 50:17
ኤር. 4:7ሕዝ 26:7
ኤር. 4:7ኢሳ 5:9፤ 6:11፤ ኤር 2:15፤ 9:11
ኤር. 4:8ኤር 6:26
ኤር. 4:92ነገ 25:5
ኤር. 4:9ኢሳ 29:9, 10
ኤር. 4:10ኤር 6:13, 14፤ 14:13፤ 23:16, 17
ኤር. 4:10ሕዝ 14:9
ኤር. 4:13ኢሳ 5:26, 28
ኤር. 4:13ዘዳ 28:49, 50፤ ሰቆ 4:19፤ ዕን 1:8
ኤር. 4:14ኢሳ 1:16፤ ሕዝ 18:31
ኤር. 4:15ኤር 8:16
ኤር. 4:172ነገ 25:1, 2
ኤር. 4:17ኢሳ 63:10፤ ሕዝ 2:3
ኤር. 4:18መዝ 107:17
ኤር. 4:19ሶፎ 1:15, 16
ኤር. 4:20ኤር 10:20
ኤር. 4:21ኤር 6:1
ኤር. 4:22ዘዳ 32:6፤ ኤር 5:21
ኤር. 4:23ኤር 9:10
ኤር. 4:23ኢሳ 5:30፤ ኢዩ 2:31
ኤር. 4:24ኢሳ 5:25
ኤር. 4:25ሶፎ 1:3
ኤር. 4:26ዘዳ 29:22, 23
ኤር. 4:27ዘሌ 26:32፤ 2ዜና 36:20, 21፤ ኢሳ 6:11፤ ኤር 10:22፤ ሕዝ 33:28
ኤር. 4:28ኢሳ 24:4፤ ኢዩ 1:10
ኤር. 4:28ኢሳ 5:30፤ ኢዩ 2:30, 31
ኤር. 4:282ነገ 23:26፤ ሕዝ 24:14
ኤር. 4:292ነገ 25:4
ኤር. 4:29ኢሳ 2:19
ኤር. 4:30ሕዝ 23:22, 26
ኤር. 4:30ሰቆ 1:2
ኤር. 4:31ሰቆ 1:17
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኤርምያስ 4:1-31

ኤርምያስ

4 “እስራኤል ሆይ፣ ብትመለስ” ይላል ይሖዋ፣

“ወደ እኔ ብትመለስ፣

አስጸያፊ ጣዖቶችህን ከፊቴ ብታስወግድ

ተንከራታች አትሆንም።+

 2 ‘በእውነት፣ በፍትሕና በጽድቅ

ሕያው ይሖዋን!’ ብለህ ብትምል፣

ብሔራት በእሱ አማካኝነት በረከት ያገኛሉ፤

በእሱም ይኮራሉ።”+

3 ይሖዋ ለይሁዳ ሰዎችና ለኢየሩሳሌም እንዲህ ይላልና፦

“ያልለማውን መሬት እረሱ፤

በእሾህ መካከልም አትዝሩ።+

 4 እናንተ የይሁዳ ሰዎችና የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች፣

ለይሖዋ ተገረዙ፤

የልባችሁንም ሸለፈት አስወግዱ፤+

አለዚያ በክፉ ሥራችሁ የተነሳ

ቁጣዬ እንደ እሳት ይነድዳል፤

ማንም ሊያጠፋው አይችልም።”+

 5 ይህን በይሁዳ ተናገሩ፤ በኢየሩሳሌምም አውጁ።

ጩኹ፤ በምድሪቱም ሁሉ ላይ ቀንደ መለከት ንፉ።+

ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ እንዲህ በሉ፦ “አንድ ላይ ተሰብሰቡ፤

ወደተመሸጉት ከተሞችም እንሽሽ።+

 6 ወደ ጽዮን የሚጠቁም ምልክት* አቁሙ።

መጠለያ ፈልጉ፤ ዝም ብላችሁም አትቁሙ።”

ከሰሜን ጥፋት ብሎም ታላቅ መዓት አመጣለሁና።+

 7 ጠላት እንደ አንበሳ ከጥሻው ውስጥ ወጥቷል፤+

ብሔራትንም የሚያጠፋው ተነስቷል።+

ምድርሽን አስፈሪ ቦታ ሊያደርግ ከቦታው ወጥቷል።

ከተሞችሽ አንድም ሰው የማይኖርባቸው የፍርስራሽ ክምር ይሆናሉ።+

 8 ስለዚህ ማቅ ልበሱ፤+

እዘኑ፤* ዋይ ዋይም በሉ፤

ምክንያቱም የሚነደው የይሖዋ ቁጣ ከእኛ አልተመለሰም።

 9 “በዚያ ቀን” ይላል ይሖዋ፣ “የንጉሡ ልብና

የመኳንንቱ ልብ ይቀልጣል፤*+

ካህናቱም ይሸበራሉ፤ ነቢያቱም ይገረማሉ።”+

10 ከዚያም እንዲህ አልኩ፦ “ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ ሆይ፣ ወዮ! ሰይፍ አንገታችን ላይ ተጋድሞ* እያለ ‘ሰላም ታገኛላችሁ’+ ብለህ ይህን ሕዝብና ኢየሩሳሌምን ፈጽሞ አታለሃል።”+

11 በዚያን ጊዜ ለዚህ ሕዝብና ለኢየሩሳሌም እንዲህ ይባላል፦

“የሚለበልብ ነፋስ በበረሃ ከሚገኙ ጠፍ ኮረብቶች ተነስቶ

ወደ ሕዝቤ ሴት ልጅ* በፍጥነት ይነፍሳል፤

ነፋሱ የሚነፍሰው እህል ለማዝራትም* ሆነ ለማጥራት አይደለም።

12 በእኔ ትእዛዝ ኃይለኛው ነፋስ ከእነዚህ ስፍራዎች ይመጣል።

አሁን በእነሱ ላይ ፍርድ አስተላልፋለሁ።

13 እነሆ፣ እሱ ዝናብ እንዳዘሉ ደመናት ይመጣል፤

ሠረገሎቹም እንደ አውሎ ነፋስ ናቸው።+

ፈረሶቹ ከንስር ይበልጥ ፈጣኖች ናቸው።+

ጠፍተናልና ወዮልን!

14 ኢየሩሳሌም ሆይ፣ እንድትድኚ ልብሽን ከክፋት ሁሉ አጥሪ።+

እስከ መቼ በውስጥሽ ክፉ ሐሳብ ይዘሽ ትኖሪያለሽ?

15 አንድ ድምፅ ከዳን ዜናውን ይናገራልና፤+

ከኤፍሬም ተራሮችም ጥፋትን ያውጃል።

16 ይህን አሳውቁ፤ አዎ ለብሔራት ተናገሩ፤

በኢየሩሳሌም ላይ አውጁ።”

“ጠባቂዎች* ከሩቅ አገር እየመጡ ነው፤

በይሁዳ ከተሞችም ላይ ይጮኻሉ።

17 ማሳ እንደሚጠብቁ ሰዎች ከሁሉም አቅጣጫ ይመጡባታል፤+

ምክንያቱም እሷ በእኔ ላይ ዓምፃለች”+ ይላል ይሖዋ።

18 “ለተከተልሽው መንገድና ለፈጸምሽው ተግባር ዋጋሽን ትቀበያለሽ።+

የሚደርስብሽ ጥፋት ምንኛ መራራ ነው፤

ወደ ልብሽ ዘልቆ ይገባልና!”

19 ወይ አበሳዬ!* ወይ አበሳዬ!

ልቤን ሥቃይ ቀስፎታል።

ልቤ በውስጤ በኃይል ይመታል።

ዝም ማለት አልችልም፤

የቀንደ መለከት ድምፅ፣

የጦርነት ማስጠንቀቂያ ድምፅ* ሰምቻለሁና።*+

20 በጥፋት ላይ ጥፋት መድረሱ ተወርቷል፤

ምድሪቱ በሙሉ ወድማለችና።

የገዛ ድንኳኖቼ በድንገት፣

የድንኳን ሸራዎቼም በቅጽበት ጠፍተዋል።+

21 ምልክቱን* የማየውና

የቀንደ መለከቱን ድምፅ የምሰማው እስከ መቼ ድረስ ነው?+

22 “ሕዝቤ ሞኝ ነውና፤+

እነሱ ለእኔ ትኩረት አይሰጡም።

ማስተዋል የሌላቸው ቂል ልጆች ናቸው።

ክፉ ነገር ለማድረግ ብልሃተኞች* ናቸው፤

መልካም ነገር ማድረግ ግን አያውቁም።”

23 ምድሪቱን አየሁ፤ እነሆም፣ ባዶና ወና ነበረች።+

ወደ ሰማያት ተመለከትኩ፤ ብርሃናቸው ጠፍቶ ነበር።+

24 ተራሮቹን አየሁ፤ እነሆ፣ ይናወጡ ነበር፤

ኮረብቶቹም ይንቀጠቀጡ ነበር።+

25 እኔም ተመለከትኩ፤ እነሆ፣ በዚያ አንድም ሰው አልነበረም፤

የሰማይ ወፎችም ሁሉ ሸሽተው ነበር።+

26 እኔም አየሁ፤ እነሆ፣ የፍራፍሬ እርሻው ምድረ በዳ ሆኖ ነበር፤

ከተሞቹም ሁሉ ፈራርሰው ነበር።+

ይህም የሆነው በይሖዋ፣

በሚነደውም ቁጣው የተነሳ ነው።

27 ይሖዋ እንዲህ ይላልና፦ “ምድሪቱ በሙሉ ባድማ ትሆናለች፤+

ሆኖም ፈጽሜ አላጠፋትም።

28 ከዚህ የተነሳ ምድሪቱ ታዝናለች፤+

በላይ ያሉት ሰማያትም ይጨልማሉ።+

ምክንያቱም እኔ ተናግሬአለሁ፤ ደግሞም ወስኛለሁ፤

ሐሳቤንም አለውጥም፤* ወደ ኋላም አልመለስም።+

29 ከፈረሰኞቹና ከቀስተኞቹ ድምፅ የተነሳ

ከተማዋ በሙሉ ትሸሻለች።+

ጥሻ ውስጥ ይገባሉ፤

ዓለቶቹም ላይ ይወጣሉ።+

ከተሞቹ ሁሉ ተትተዋል፤

የሚኖርባቸውም ሰው የለም።”

30 ለጥፋት ተዳርገሻል፤ ታዲያ ምን ታደርጊ ይሆን?

ደማቅ ቀይ ልብስ ትጎናጸፊ፣

በወርቅ ጌጣጌጦች ታጌጪና

ዓይኖችሽን ትኳዪ ነበር።

ይሁንና ትዋቢ የነበረው እንዲያው በከንቱ ነው፤+

በፍትወት ስሜት ይከተሉሽ የነበሩት ትተውሻልና፤

አሁን ሕይወትሽን* ይሿታል።+

31 እንደታመመች ሴት ድምፅ፣

የመጀመሪያ ልጇንም ለመውለድ እንደምታምጥ ሴት ያለ የጭንቅ ድምፅ፣

ደግሞም ትንፋሽ አጥሯት ቁና ቁና የምትተነፍሰውን የጽዮን ሴት ልጅ ድምፅ ሰምቻለሁና።

እሷም እጆቿን ዘርግታ+

“ወዮልኝ! ከገዳዮች የተነሳ ዝያለሁና”* ትላለች።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ