የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 2 ዜና መዋዕል 1
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

2 ዜና መዋዕል የመጽሐፉ ይዘት

      • ሰለሞን ጥበብ እንዲሰጠው ጠየቀ (1-12)

      • የሰለሞን ሀብት (13-17)

2 ዜና መዋዕል 1:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ዜና 29:25፤ መክ 2:9፤ ማቴ 6:28, 29፤ 12:42

2 ዜና መዋዕል 1:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 3:4፤ 1ዜና 21:29

2 ዜና መዋዕል 1:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ዜና 13:5
  • +1ዜና 16:1

2 ዜና መዋዕል 1:5

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በዚያ አምላክን ይጠይቁ ነበር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 31:2-5
  • +ዘፀ 38:1, 2

2 ዜና መዋዕል 1:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 3:4

2 ዜና መዋዕል 1:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 3:5-9

2 ዜና መዋዕል 1:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 7:8
  • +1ዜና 28:5፤ መዝ 89:28, 29

2 ዜና መዋዕል 1:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 7:12፤ 1ዜና 28:6፤ መዝ 132:11
  • +ዘፍ 13:14, 16

2 ዜና መዋዕል 1:10

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “በዚህ ሕዝብ ፊት መውጣትና መግባት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ምሳሌ 2:6፤ ያዕ 1:5
  • +መዝ 72:1, 2

2 ዜና መዋዕል 1:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍስ።”

  • *

    ቃል በቃል “ብዙ ቀናት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 3:10-13, 28

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    12/1/2005፣ ገጽ 19

2 ዜና መዋዕል 1:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ዜና 29:25፤ 2ዜና 9:22፤ መክ 2:9

2 ዜና መዋዕል 1:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 3:4

2 ዜና መዋዕል 1:14

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ፈረሰኞችን።”

  • *

    ወይም “ፈረሰኞች።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 17:16፤ 1ነገ 4:26
  • +2ዜና 8:5, 6
  • +2ዜና 9:25

2 ዜና መዋዕል 1:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ነገ 10:21
  • +1ነገ 10:27፤ 2ዜና 9:27

2 ዜና መዋዕል 1:16

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “ከግብፅና ከቀዌ ያስመጣቸው ነበሩ፤ የንጉሡ ነጋዴዎች ከቀዌ አንዴ በተተመነው ዋጋ ይገዟቸው ነበር” ማለትም ሊሆን ይችላል። ቀዌ ኪልቅያን ልታመለክት ትችላለች።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 9:28
  • +1ነገ 10:28, 29

ተዛማጅ ሐሳብ

2 ዜና 1:11ዜና 29:25፤ መክ 2:9፤ ማቴ 6:28, 29፤ 12:42
2 ዜና 1:31ነገ 3:4፤ 1ዜና 21:29
2 ዜና 1:41ዜና 13:5
2 ዜና 1:41ዜና 16:1
2 ዜና 1:5ዘፀ 31:2-5
2 ዜና 1:5ዘፀ 38:1, 2
2 ዜና 1:61ነገ 3:4
2 ዜና 1:71ነገ 3:5-9
2 ዜና 1:82ሳሙ 7:8
2 ዜና 1:81ዜና 28:5፤ መዝ 89:28, 29
2 ዜና 1:92ሳሙ 7:12፤ 1ዜና 28:6፤ መዝ 132:11
2 ዜና 1:9ዘፍ 13:14, 16
2 ዜና 1:10ምሳሌ 2:6፤ ያዕ 1:5
2 ዜና 1:10መዝ 72:1, 2
2 ዜና 1:111ነገ 3:10-13, 28
2 ዜና 1:121ዜና 29:25፤ 2ዜና 9:22፤ መክ 2:9
2 ዜና 1:131ነገ 3:4
2 ዜና 1:14ዘዳ 17:16፤ 1ነገ 4:26
2 ዜና 1:142ዜና 8:5, 6
2 ዜና 1:142ዜና 9:25
2 ዜና 1:151ነገ 10:21
2 ዜና 1:151ነገ 10:27፤ 2ዜና 9:27
2 ዜና 1:162ዜና 9:28
2 ዜና 1:161ነገ 10:28, 29
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
2 ዜና መዋዕል 1:1-17

ሁለተኛ ዜና መዋዕል

1 የዳዊት ልጅ ሰለሞን ንግሥናውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያጠናከረ ሄደ፤ አምላኩ ይሖዋም ከእሱ ጋር ስለነበር እጅግ ገናና አደረገው።+

2 ሰለሞን ለእስራኤል ሁሉ፣ ለሺህ አለቆች፣ ለመቶ አለቆች፣ ለፈራጆችና የአባቶች ቤቶች መሪዎች ለሆኑት በመላው እስራኤል ለሚገኙት አለቆች ሁሉ መልእክት ላከ። 3 ከዚያም ሰለሞንና መላው ጉባኤ በገባኦን+ ወደሚገኘው ኮረብታ ሄዱ፤ ምክንያቱም የይሖዋ አገልጋይ ሙሴ በምድረ በዳ የሠራው የእውነተኛው አምላክ የመገናኛ ድንኳን የሚገኘው በዚያ ነበር። 4 ይሁን እንጂ ዳዊት የእውነተኛውን አምላክ ታቦት ከቂርያትየአሪም+ እሱ ወዳዘጋጀለት ስፍራ አምጥቶት ነበር፤ በኢየሩሳሌምም ድንኳን ተክሎለት ነበር።+ 5 የሁር ልጅ የዖሪ ልጅ ባስልኤል+ የሠራው የመዳብ መሠዊያ+ በይሖዋ የማደሪያ ድንኳን ፊት ይገኝ ነበር፤ ሰለሞንና ጉባኤውም በመሠዊያው ፊት ይጸልዩ ነበር።* 6 ሰለሞንም በዚያ በይሖዋ ፊት መባ አቀረበ፤ በመገናኛው ድንኳን በሚገኘው የመዳብ መሠዊያ ላይ 1,000 የሚቃጠሉ መባዎችን አቀረበ።+

7 በዚያ ሌሊት አምላክ ለሰለሞን ተገልጦ “እንድሰጥህ የምትፈልገውን ጠይቅ” አለው።+ 8 በዚህ ጊዜ ሰለሞን አምላክን እንዲህ አለው፦ “ለአባቴ ለዳዊት ጥልቅ የሆነ ታማኝ ፍቅር አሳይተኸዋል፤+ በእሱም ምትክ አንግሠኸኛል።+ 9 አሁንም ይሖዋ አምላክ ሆይ፣ ለአባቴ ለዳዊት የገባኸው ቃል ይፈጸም፤+ እንደ ምድር አፈር እጅግ ብዙ በሆነ ሕዝብ+ ላይ አንግሠኸኛልና። 10 ይህን ሕዝብ መምራት* እንድችል ጥበብና እውቀት ስጠኝ፤+ አለዚያማ ይህን ታላቅ ሕዝብህን ማን ሊዳኝ ይችላል?”+

11 ከዚያም አምላክ ሰለሞንን እንዲህ አለው፦ “የልብህ መሻት ይህ ስለሆነ ደግሞም ብልጽግና፣ ሀብትና ክብር ወይም የሚጠሉህን ሰዎች ሞት* አሊያም ረጅም ዕድሜ* ስላልተመኘህ፣ ይልቁንም አንተን ንጉሥ አድርጌ የሾምኩበትን ሕዝቤን ማስተዳደር እንድትችል ጥበብና እውቀት ስለጠየቅክ፣+ 12 ጥበብና እውቀት ይሰጥሃል፤ ከዚህም ሌላ ከአንተ በፊት የነበረ ማንኛውም ንጉሥ ያላገኘውን፣ ከአንተም በኋላ የሚነሳ የትኛውም ንጉሥ የማያገኘውን ብልጽግና፣ ሀብትና ክብር እሰጥሃለሁ።”+

13 ሰለሞንም በገባኦን+ ኮረብታ ከሚገኘው ከመገናኛው ድንኳን ፊት ወጥቶ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ፤ በእስራኤልም ላይ ነገሠ። 14 ሰለሞን ሠረገሎችንና ፈረሶችን* መሰብሰቡን ቀጠለ፤ እሱም 1,400 ሠረገሎችና 12,000 ፈረሶች* ነበሩት፤+ እነሱንም በሠረገላ ከተሞችና+ በኢየሩሳሌም በንጉሡ አቅራቢያ አኖራቸው።+ 15 ንጉሡ ብርና ወርቅ በየቦታው እንደሚገኝ ድንጋይ እስኪሆን ድረስ በኢየሩሳሌም እንዲበዛ አደረገ፤+ አርዘ ሊባኖሱንም ከብዛቱ የተነሳ በሸፌላ እንደሚገኘው የሾላ ዛፍ አደረገው።+ 16 የሰለሞን ፈረሶች ከግብፅ ያስመጣቸው ነበሩ፤+ የንጉሡ ነጋዴዎችም የፈረሶቹን መንጋ አንዴ በተተመነው ዋጋ ይገዙ ነበር።*+ 17 ከግብፅ የሚመጣው እያንዳንዱ ሠረገላ 600 የብር ሰቅል ያወጣ ነበር፤ አንድ ፈረስ ደግሞ 150 ሰቅል ያወጣል፤ እነሱ ደግሞ በተራቸው ለሂታውያን ነገሥታትና ለሶርያ ነገሥታት ሁሉ ሠረገሎችንና ፈረሶችን ይሸጡ ነበር።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ