የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 8
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኢሳይያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • የአሦር ወረራ (1-8)

        • ማኸር-ሻላል-ሃሽ-ባዝ (1-4)

      • አትፍሩ፤ “አምላክ ከእኛ ጋር ነው” (9-17)

      • ኢሳይያስና ልጆቹ ምልክት ሆነው ያገለግላሉ (18)

      • አጋንንትን ከመጠየቅ ይልቅ ሕጉን ተመልከቱ (19-22)

ኢሳይያስ 8:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ሟች በሆነ ሰው ብዕር።”

  • *

    “ወደ ምርኮው ፈጥኖ መሄድ፣ ወደ ብዝበዛው ፈጥኖ መምጣት” የሚል ትርጉም ሊኖረው ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 30:8

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የስብሰባው አስተዋጽኦ የማመሣከሪያ ጽሑፎች፣ 12/2016፣ ገጽ 1

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 111-112

ኢሳይያስ 8:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ይመሥክሩልኝ፤ ቃላቸውን ይስጡልኝ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 16:10

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 111-112

ኢሳይያስ 8:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    የኢሳይያስን ሚስት ታመለክታለች።

  • *

    ቃል በቃል “ወደ ነቢዪቱ ቀረብኩ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 8:18

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    11/15/2013፣ ገጽ 16-17

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 8, 112

ኢሳይያስ 8:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 15:29፤ 16:8, 9፤ 17:6፤ ኢሳ 7:16፤ 17:1

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 112

ኢሳይያስ 8:6

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ሺሎአ የውኃ ቦይ ነበር።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 17:16፤ ኤር 17:13
  • +ኢሳ 7:1

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 113-114

ኢሳይያስ 8:7

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ኤፍራጥስን ያመለክታል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 17:5፤ 18:9

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 113-114

ኢሳይያስ 8:8

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ኢሳ 7:14ን ተመልከት።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 28:19, 20፤ ኢሳ 7:17, 20፤ 10:28-32
  • +ኢሳ 7:14፤ ማቴ 1:23

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 113-114, 116

ኢሳይያስ 8:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ታጠቁ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 32:21

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 114

ኢሳይያስ 8:10

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “አምላክ ከእኛ ጋር ነው” ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል ኢማኑኤል የሚለው ነው። ኢሳ 7:14ንና 8:8ን ተመልከት።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 20:1፤ መዝ 44:3

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 114

ኢሳይያስ 8:11

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 114-115

ኢሳይያስ 8:12

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 114-115

ኢሳይያስ 8:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 10:3፤ 22:32
  • +መክ 12:13፤ ማቴ 10:28

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 114-115

ኢሳይያስ 8:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ማቴ 21:42, 44፤ ሉቃስ 20:17, 18፤ ሮም 9:31-33፤ 1ቆሮ 1:23፤ 1ጴጥ 2:7, 8

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው፣ ርዕስ 146

    መጠበቂያ ግንብ፣

    10/1/2008፣ ገጽ 5

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 115

    “ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ”፣ ገጽ 123፣ 253

ኢሳይያስ 8:15

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 115

ኢሳይያስ 8:16

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የምሥክርነት ቃል።”

  • *

    ወይም “መመሪያውን፤ ትምህርቱን።”

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 115-116

ኢሳይያስ 8:17

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በጉጉት እጠብቃለሁ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 31:16, 17፤ ሚክ 3:4
  • +መዝ 33:20

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 115-116

ኢሳይያስ 8:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዕብ 2:13
  • +ኢሳ 7:14, 16፤ 8:3, 4

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 2፣ ገጽ 407

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 116

ኢሳይያስ 8:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 20:6፤ ዘዳ 18:10, 11፤ መዝ 146:4፤ መክ 9:5, 10

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    ለዘላለም በደስታ ኑር!፣ ትምህርት 29

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 118-121

ኢሳይያስ 8:20

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “የምሥክርነት ቃሉን።”

  • *

    ቃል በቃል “አይነጋላቸውም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ምሳሌ 4:19

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 121-123

ኢሳይያስ 8:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 28:15, 48

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    8/15/2013፣ ገጽ 11

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 123-124

ኢሳይያስ 8:22

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 124

ተዛማጅ ሐሳብ

ኢሳ. 8:1ኢሳ 30:8
ኢሳ. 8:22ነገ 16:10
ኢሳ. 8:3ኢሳ 8:18
ኢሳ. 8:42ነገ 15:29፤ 16:8, 9፤ 17:6፤ ኢሳ 7:16፤ 17:1
ኢሳ. 8:62ነገ 17:16፤ ኤር 17:13
ኢሳ. 8:6ኢሳ 7:1
ኢሳ. 8:72ነገ 17:5፤ 18:9
ኢሳ. 8:82ዜና 28:19, 20፤ ኢሳ 7:17, 20፤ 10:28-32
ኢሳ. 8:8ኢሳ 7:14፤ ማቴ 1:23
ኢሳ. 8:92ዜና 32:21
ኢሳ. 8:10ዘዳ 20:1፤ መዝ 44:3
ኢሳ. 8:13ዘሌ 10:3፤ 22:32
ኢሳ. 8:13መክ 12:13፤ ማቴ 10:28
ኢሳ. 8:14ማቴ 21:42, 44፤ ሉቃስ 20:17, 18፤ ሮም 9:31-33፤ 1ቆሮ 1:23፤ 1ጴጥ 2:7, 8
ኢሳ. 8:17ዘዳ 31:16, 17፤ ሚክ 3:4
ኢሳ. 8:17መዝ 33:20
ኢሳ. 8:18ዕብ 2:13
ኢሳ. 8:18ኢሳ 7:14, 16፤ 8:3, 4
ኢሳ. 8:19ዘሌ 20:6፤ ዘዳ 18:10, 11፤ መዝ 146:4፤ መክ 9:5, 10
ኢሳ. 8:20ምሳሌ 4:19
ኢሳ. 8:21ዘዳ 28:15, 48
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኢሳይያስ 8:1-22

ኢሳይያስ

8 ይሖዋ እንዲህ አለኝ፦ “አንድ ትልቅ ጽላት+ ወስደህ በብዕር* ‘ማኸር-ሻላል-ሃሽ-ባዝ’* ብለህ ጻፍ። 2 ታማኝ ምሥክሮች የሆኑት ካህኑ ኦርዮና+ የበራክዩ ልጅ ዘካርያስ ደግሞ የጽሑፍ ማረጋገጫ ይስጡኝ።”*

3 እኔም ከነቢዪቱ* ጋር ተገናኘሁ፤* እሷም ፀነሰች፤ በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች።+ ከዚያም ይሖዋ እንዲህ አለኝ፦ “ስሙን ማኸር-ሻላል-ሃሽ-ባዝ ብለህ ጥራው፤ 4 ልጁ ‘አባዬ!’ እና ‘እማዬ!’ ብሎ መጥራት ከመቻሉ በፊት የደማስቆ ሀብትና የሰማርያ ምርኮ በአሦር ንጉሥ ፊት ይወሰዳል።”+

5 ይሖዋ በድጋሚ እንዲህ አለኝ፦

 6 “ይህ ሕዝብ ቀስ ብለው የሚወርዱትን የሺሎአ* ውኃዎች ንቆ+

በረጺንና በረማልያህ+ ልጅ ሐሴት ስላደረገ

 7 እነሆ፣ ይሖዋ ብርቱ የሆኑትንና ከፍተኛ መጠን ያላቸውን የወንዙን* ውኃዎች ይኸውም

የአሦርን ንጉሥና+ ክብሩን ሁሉ

በእነሱ ላይ ያመጣባቸዋል።

እሱም የውኃ መውረጃዎቹን ሁሉ ሞልቶ ይፈስሳል፤

ዳርቻዎቹንም ሁሉ ያጥለቀልቃል፤

 8 ይሁዳንም ጠራርጎ ይሄዳል።

አካባቢውን እያጥለቀለቀ በማለፍ እስከ አንገት ይደርሳል፤+

አማኑኤል*+ ሆይ፣ የተዘረጉት ክንፎቹ

ምድርህን ከዳር እስከ ዳር ይሸፍናሉ!”

 9 እናንተ ሕዝቦች፣ ጉዳት አድርሱባቸው፤ ሆኖም ድምጥማጣችሁ ይጠፋል።

ራቅ ባሉ የምድር ክፍሎች የምትኖሩ ሁሉ አዳምጡ!

ለውጊያ ተዘጋጁ፤* ነገር ግን ድምጥማጣችሁ ይጠፋል!+

ለውጊያ ተዘጋጁ፤ ነገር ግን ድምጥማጣችሁ ይጠፋል!

10 ዕቅድ አውጡ፤ ይሁንና ይጨናገፋል!

የፈለጋችሁትን ተናገሩ፤ ሆኖም አይሳካም፤

አምላክ ከእኛ ጋር ነውና!*+

11 ይሖዋ ብርቱ እጁን በእኔ ላይ አድርጎ የዚህን ሕዝብ መንገድ እንዳልከተል ለማስጠንቀቅ እንዲህ አለኝ፦

12 “ይህ ሕዝብ ‘ሴራ እንጠንስስ!’ ሲል እናንተ ‘በሴራው ተባበሩ!’ አትበሉ፤

እነሱ የሚያስፈራቸውን ነገር አትፍሩ፤

አትንቀጥቀጡለትም።

13 ቅዱስ አድርጋችሁ ልትመለከቱ የሚገባው የሠራዊት ጌታ ይሖዋን ነው፤+

ልትፈሩ የሚገባው እሱን ነው፤

እንዲሁም ልትንቀጠቀጡ የሚገባው ለእሱ ነው።”+

14 እሱ እንደ መቅደስ ይሆናል፤

ለሁለቱ የእስራኤል ቤቶች ግን

እንደሚያሰናክል ድንጋይና

እንደሚያደናቅፍ ዓለት፣+

ለኢየሩሳሌም ነዋሪዎችም

እንደ ወጥመድና እንደ አሽክላ ይሆንባቸዋል።

15 ከእነሱ መካከል ብዙዎቹ ይደናቀፋሉ፣ ይወድቃሉ፣ ይሰበራሉ፤

ወጥመድ ውስጥ ገብተው ይያዛሉ።

16 በጽሑፍ የሰፈረውን ማረጋገጫ* ጠቅልለው፤

ሕጉን* በደቀ መዛሙርቴ መካከል አሽገው!

17 እኔም ፊቱን ከያዕቆብ ቤት የሰወረውን+ ይሖዋን እጠባበቃለሁ፤*+ በእሱም ተስፋ አደርጋለሁ።

18 እነሆ፣ እኔና ይሖዋ የሰጠኝ ልጆች+ በጽዮን ተራራ ከሚኖረው ከሠራዊት ጌታ ከይሖዋ ለእስራኤል እንደተሰጡ ምልክቶችና+ ተአምራት ነን።

19 እነሱም “የሚያነበንቡትንና የሚያንሾካሹኩትን መናፍስት ጠሪዎች ወይም ጠንቋዮች ጠይቁ” ቢሏችሁ፣ አንድ ሕዝብ መጠየቅ ያለበት የራሱን አምላክ አይደለም? ስለ ሕያዋንስ ሙታንን መጠየቁ ተገቢ ነው?+ 20 ከዚህ ይልቅ ሕጉንና የማረጋገጫ ሰነዱን* መመርመር ይገባቸዋል!

ከዚህ ቃል ጋር የሚስማማ ነገር ሳይናገሩ ሲቀሩ ብርሃን አይበራላቸውም።*+ 21 እያንዳንዱም ተጎሳቁሎና ተርቦ በምድሪቱ ላይ ይንከራተታል፤+ ከመራቡና ከመበሳጨቱ የተነሳ ወደ ላይ እያየ ንጉሡንና አምላኩን ይረግማል። 22 ከዚያም ወደ ምድር ይመለከታል፤ የሚያየውም ነገር ጭንቀትና ጨለማ፣ ግራ የሚያጋባ ሁኔታ፣ አስቸጋሪ ወቅትና ብርሃን የሌለበት ፅልማሞት ብቻ ይሆናል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ