የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፍጥረት 44
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘፍጥረት የመጽሐፉ ይዘት

      • የዮሴፍ የብር ጽዋ በቢንያም ከረጢት ውስጥ ተገኘ (1-17)

      • ይሁዳ ስለ ቢንያም ተማጸነ (18-34)

ዘፍጥረት 44:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:25

ዘፍጥረት 44:5

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    2/1/2006፣ ገጽ 31

    1/15/2004፣ ገጽ 29

ዘፍጥረት 44:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 43:12

ዘፍጥረት 44:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 44:2

ዘፍጥረት 44:14

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 43:8፤ 44:32
  • +ዘፍ 37:7, 9

ዘፍጥረት 44:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 44:5

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    መጠበቂያ ግንብ፣

    2/1/2006፣ ገጽ 31

ዘፍጥረት 44:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:18, 28፤ 42:21, 22

ዘፍጥረት 44:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 44:9

ዘፍጥረት 44:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 41:44፤ 45:8

ዘፍጥረት 44:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:13፤ 43:7
  • +ዘፍ 37:31-34
  • +ዘፍ 35:18, 19

ዘፍጥረት 44:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:15፤ 43:29

ዘፍጥረት 44:22

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:38

ዘፍጥረት 44:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 42:20

ዘፍጥረት 44:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 43:2

ዘፍጥረት 44:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 43:5

ዘፍጥረት 44:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 29:18፤ 30:22-24፤ 35:18, 19፤ 46:19

ዘፍጥረት 44:28

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:33

ዘፍጥረት 44:29

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ሲኦል።” የሰው ልጆችን ሁሉ መቃብር ያመለክታል። የቃላት መፍቻውን ተመልከት።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 37:34, 35፤ 42:38፤ መዝ 88:3
  • +መዝ 16:10፤ መክ 9:10፤ ሆሴዕ 13:14፤ ሥራ 2:27፤ ራእይ 20:13

ዘፍጥረት 44:30

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍስ።”

  • *

    ወይም “ነፍስ።”

ዘፍጥረት 44:31

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ሲኦል።” የሰው ልጆችን ሁሉ መቃብር ያመለክታል። የቃላት መፍቻውን ተመልከት።

ዘፍጥረት 44:32

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 43:9

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘፍ. 44:1ዘፍ 42:25
ዘፍ. 44:8ዘፍ 43:12
ዘፍ. 44:12ዘፍ 44:2
ዘፍ. 44:14ዘፍ 43:8፤ 44:32
ዘፍ. 44:14ዘፍ 37:7, 9
ዘፍ. 44:15ዘፍ 44:5
ዘፍ. 44:16ዘፍ 37:18, 28፤ 42:21, 22
ዘፍ. 44:17ዘፍ 44:9
ዘፍ. 44:18ዘፍ 41:44፤ 45:8
ዘፍ. 44:20ዘፍ 42:13፤ 43:7
ዘፍ. 44:20ዘፍ 37:31-34
ዘፍ. 44:20ዘፍ 35:18, 19
ዘፍ. 44:21ዘፍ 42:15፤ 43:29
ዘፍ. 44:22ዘፍ 42:38
ዘፍ. 44:23ዘፍ 42:20
ዘፍ. 44:25ዘፍ 43:2
ዘፍ. 44:26ዘፍ 43:5
ዘፍ. 44:27ዘፍ 29:18፤ 30:22-24፤ 35:18, 19፤ 46:19
ዘፍ. 44:28ዘፍ 37:33
ዘፍ. 44:29ዘፍ 37:34, 35፤ 42:38፤ መዝ 88:3
ዘፍ. 44:29መዝ 16:10፤ መክ 9:10፤ ሆሴዕ 13:14፤ ሥራ 2:27፤ ራእይ 20:13
ዘፍ. 44:32ዘፍ 43:9
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
  • 32
  • 33
  • 34
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘፍጥረት 44:1-34

ዘፍጥረት

44 ከዚህ በኋላ ዮሴፍ የቤቱ ኃላፊ የሆነውን ሰው እንዲህ ሲል አዘዘው፦ “የቻሉትን ያህል እህል በየከረጢቶቻቸው ሙላላቸው፤ የእያንዳንዳቸውንም ገንዘብ በየከረጢቶቻቸው አፍ ላይ አድርገው።+ 2 ሆኖም የእኔን ጽዋ ይኸውም የብር ጽዋዬን ውሰድና እህል ለመግዛት ካመጣው ገንዘብ ጋር አድርገህ በትንሹ ወንድማቸው ከረጢት አፍ ላይ አድርገው።” እሱም ልክ ዮሴፍ እንዳዘዘው አደረገ።

3 ሰዎቹም ማለዳ ላይ ጎህ ሲቀድ ከነአህዮቻቸው ተሸኙ። 4 እነሱም ከከተማዋ ብዙም ርቀው ሳይሄዱ ዮሴፍ የቤቱ ኃላፊ የሆነውን ሰው እንዲህ አለው፦ “ተነስ! ሰዎቹን ተከታተላቸው! ስትደርስባቸውም እንዲህ በላቸው፦ ‘ለተደረገላችሁ መልካም ነገር ክፉ የመለሳችሁት ለምንድን ነው? 5 ይህ ጌታዬ የሚጠጣበትና የሚጠነቁልበት ጽዋ አይደለም? የፈጸማችሁት ድርጊት በጣም አሳፋሪ ነው።’”

6 እሱም ተከታትሎ ደረሰባቸውና ልክ እንደተባለው አላቸው። 7 እነሱ ግን እንዲህ አሉት፦ “ጌታዬ እንዲህ ያለ ነገር የሚናገረው ለምንድን ነው? አገልጋዮችህ እንዲህ ያለ ነገር ያደርጋሉ ማለት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው። 8 በከረጢቶቻችን አፍ ላይ ያገኘነውን ገንዘብ እንኳ ከከነአን ምድር ድረስ ይዘን ወደ አንተ መጥተን የለም?+ ታዲያ ከጌታህ ቤት ብር ወይም ወርቅ እንዴት እንሰርቃለን? 9 ከእኛ ከባሪያዎችህ መካከል የተገኘበት ቢኖር ያ ሰው ይገደል፤ የቀረነውም ለጌታዬ ባሪያዎች እንሆናለን።” 10 እሱም “እሺ፣ እንዳላችሁት ይሁን፤ ጽዋው የተገኘበት ሰው ባሪያዬ ይሆናል፤ የቀራችሁት ግን ነፃ ትሆናላችሁ” አላቸው። 11 ከዚያም እያንዳንዳቸው ወዲያውኑ ከረጢታቸውን መሬት አውርደው መፍታት ጀመሩ። 12 እሱም ከታላቁ ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ በጥንቃቄ ፈተሸ። በመጨረሻም ጽዋው በቢንያም ከረጢት ውስጥ ተገኘ።+

13 በዚህ ጊዜ ልብሳቸውን ቀደዱ፤ እያንዳንዳቸውም ጓዛቸውን መልሰው በአህዮቻቸው ላይ በመጫን ወደ ከተማዋ ተመለሱ። 14 ይሁዳና+ ወንድሞቹ ወደ ዮሴፍ ቤት ሲገቡ ዮሴፍ ገና ከቤት አልወጣም ነበር፤ እነሱም በፊቱ መሬት ላይ ተደፉ።+ 15 ዮሴፍም “ይህ ያደረጋችሁት ነገር ምንድን ነው? እንደ እኔ ያለ ሰው ማንኛውንም ነገር በጥንቆላ የማወቅ ችሎታ እንዳለው አታውቁም?” አላቸው።+ 16 በዚህ ጊዜ ይሁዳ እንዲህ አለ፦ “እንግዲህ ለጌታዬ ምን ማለት እንችላለን? ምንስ አፍ አለን? ጻድቅ መሆናችንን እንዴት ማረጋገጥ እንችላለን? እውነተኛው አምላክ ባሪያዎችህ የፈጸሙትን ስህተት አጋልጧል።+ እንግዲህ እኛም ሆን ጽዋው የተገኘበት ሰው ለጌታዬ ባሪያዎች እንሆናለን!” 17 እሱ ግን እንዲህ አላቸው፦ “ይህንማ ፈጽሞ አላደርገውም! ባሪያዬ የሚሆነው ጽዋው የተገኘበት ሰው ነው።+ የቀራችሁት ግን ወደ አባታችሁ በሰላም ሂዱ።”

18 ይሁዳም ወደ እሱ ቀርቦ እንዲህ አለው፦ “እባክህ ጌታዬ እማጸንሃለሁ፤ ባሪያህ አንዲት ቃል ብቻ ይናገር፤ ጌታዬም ይስማው፤ እባክህ በባሪያህ ላይ አትቆጣ፤ ምክንያቱም አንተ ልክ እንደ ፈርዖን ነህ።+ 19 ጌታዬ እኛን ባሪያዎቹን ‘አባት ወይም ወንድም አላችሁ?’ በማለት ጠይቆን ነበር። 20 እኛም ለጌታዬ እንዲህ ስንል መለስንለት፦ ‘አረጋዊ አባት አለን፤ እንዲሁም በስተርጅናው የወለደው የሁላችንም ታናሽ የሆነ ወንድም አለን።+ ወንድሙ ግን ሞቷል፤+ በመሆኑም ከአንድ እናት ከተወለዱት መካከል የቀረው እሱ ብቻ ነው፤+ አባቱም በጣም ይወደዋል።’ 21 ከዚያም አንተ እኛን ባሪያዎችህን ‘እንዳየው ወደ እኔ አምጡት’ አልከን።+ 22 እኛ ግን ጌታዬን ‘ልጁ ከአባቱ ሊለይ አይችልም። ከተለየው ደግሞ አባቱ ያለጥርጥር ይሞታል’+ አልነው። 23 አንተም እኛን ባሪያዎችህን ‘ትንሹን ወንድማችሁን ይዛችሁት ካልመጣችሁ ከእንግዲህ ፊቴን አታዩም’ አልከን።+

24 “በመሆኑም ወደ ባሪያህ ወደ አባታችን ሄደን የጌታዬን ቃል ነገርነው። 25 ከጊዜ በኋላም አባታችን ‘ተመልሳችሁ ሂዱና ጥቂት እህል ግዙልን’ አለን።+ 26 እኛ ግን እንዲህ አልነው፦ ‘ወደዚያ መሄድ አንችልም። ትንሹ ወንድማችን ከእኛ ጋር ካልሄደ የሰውየውን ፊት ማየት ስለማንችል ትንሹ ወንድማችን አብሮን የሚሄድ ከሆነ ወደዚያ እንወርዳለን።’+ 27 በዚህ ጊዜ ባሪያህ አባታችን እንዲህ አለን፦ ‘ሚስቴ ከሁለት ወንዶች ልጆች ሌላ ምንም እንዳልወለደችልኝ እናንተ ራሳችሁ በሚገባ ታውቃላችሁ።+ 28 ሆኖም አንዱ እንደወጣ በመቅረቱ “መቼም አውሬ ቦጫጭቆት መሆን አለበት!” አልኩ፤+ ይኸው ከዚያን ጊዜ ወዲህ አይቼው አላውቅም። 29 ይሄኛውንም ልጅ ከእኔ ለይታችሁ ብትወስዱትና አደጋ ደርሶበት ቢሞት ሽበቴን በሥቃይ+ ወደ መቃብር*+ ታወርዱታላችሁ።’

30 “እንግዲህ ወደ ባሪያህ ወደ አባቴ ስመለስ ልጁ ከእኛ ጋር ከሌለ፣ የአባታችን ሕይወት* ከልጁ ሕይወት* ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ስለሆነ 31 አባታችን ልጁ አብሮን አለመኖሩን ሲያይ ይሞታል፤ ባሪያዎችህም የባሪያህን የአባታችንን ሽበት በሐዘን ወደ መቃብር* ያወርዱታል። 32 እኔ ባሪያህ ‘ልጁን ወደ አንተ መልሼ ባላመጣው በአባቴ ፊት ለዘላለም በደለኛ ልሁን’ ብዬ ለአባቴ ቃል ገብቻለሁ።+ 33 ስለዚህ እባክህ ልጁ ከወንድሞቹ ጋር እንዲሄድ እኔ ባሪያህ በልጁ ፋንታ እዚሁ ቀርቼ ለጌታዬ ባሪያ ልሁን። 34 ልጁን ሳልይዝ እንዴት ወደ አባቴ እመለሳለሁ? በአባቴ ላይ እንዲህ ያለ መከራ ሲደርስ ማየት አልችልም!”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ