ኢዮብ
35 ኤሊሁ እንዲህ ሲል መልስ መስጠቱን ቀጠለ፦
3 ደግሞም ‘ይህ ለአንተ* ምን ለውጥ ያመጣል?
ኃጢአት ብሠራ ኖሮ ከዚህ የከፋ ነገር ይደርስብኝ ነበር?’ ብለሃልና።+
4 ለአንተና አብረውህ ላሉት ወዳጆችህ፣+
መልስ እሰጣለሁ።
6 ኃጢአት ብትሠራ እሱን ምን ትጎዳዋለህ?+
በደልህ ቢበዛ እሱን ምን ታደርገዋለህ?+
8 ክፋት ብትሠራ የምትጎዳው እንደ አንተ ያለውን ሰው ብቻ ነው፤
ጽድቅህም የሚጠቅመው የሰውን ልጅ ነው።
12 በክፉዎች ኩራት የተነሳ ሰዎች ይጮኻሉ፤
ሆኖም እሱ አይመልስላቸውም።+
14 አላየሁትም ብለህ ቅሬታ እያሰማህ፣ አንተንማ እንዴት ይስማህ!+
ጉዳይህ በእሱ ፊት ነው፤ ስለዚህ እሱን በትዕግሥት ተጠባበቅ።+
16 ኢዮብ አፉን የሚከፍተው በከንቱ ነው፤
እውቀት ሳይኖረው ብዙ ይናገራል።”+