የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 18
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኢሳይያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • ለኢትዮጵያ የተነገረ የማስጠንቀቂያ መልእክት (1-7)

ኢሳይያስ 18:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 20:3, 4፤ ሕዝ 30:4

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 199

ኢሳይያስ 18:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ወደተመዘዘና ወደሚያብረቀርቅ ሕዝብ።”

  • *

    ወይም “ሌሎችን ወደሚረግጥ ታላቅ ጥንካሬ ያለው ብሔር።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 12:2, 3፤ 14:9፤ 16:8

ኢሳይያስ 18:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ለምልክት እንደሚተከል ምሰሶ።”

ኢሳይያስ 18:4

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “ከተመሠረተው ስፍራዬ” ማለትም ሊሆን ይችላል።

ኢሳይያስ 18:5

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 199-200

ኢሳይያስ 18:7

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “የተመዘዘና የሚያብረቀርቅ ሕዝብ።”

  • *

    ወይም “ሌሎችን የሚረግጥ ታላቅ ጥንካሬ ያለው ብሔርና።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 8:18፤ 24:23

ማውጫዎች

  • የምርምር መርጃ

    የኢሳይያስ ትንቢት 1፣ ገጽ 200

ተዛማጅ ሐሳብ

ኢሳ. 18:1ኢሳ 20:3, 4፤ ሕዝ 30:4
ኢሳ. 18:22ዜና 12:2, 3፤ 14:9፤ 16:8
ኢሳ. 18:7ኢሳ 8:18፤ 24:23
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኢሳይያስ 18:1-7

ኢሳይያስ

18 በክንፋቸው ጥዝ የሚል ድምፅ የሚያሰሙ ጥቃቅን ነፍሳት ላሉባት

በኢትዮጵያ ወንዞች አካባቢ ለምትገኝ ምድር ወዮላት!+

 2 ይህች ምድር በባሕር ላይ፣

በደንገል ጀልባ ውኃዎችን አቋርጠው የሚሄዱ መልእክተኞችን እንዲህ በማለት ትልካለች፦

“እናንተ ፈጣን መልእክተኞች፣

ረጃጅም የሆኑና ለስላሳ ቆዳ ያላቸው ሰዎች ወደሚገኙበት ብሔር፣*

ከቅርብም ሆነ ከሩቅ ወደሚፈራ ሕዝብ፣+

ጥንካሬ ወዳለውና ድል አድራጊ ወደሆነው*

እንዲሁም መሬቱ በወንዞች ተጠርጎ ወደተወሰደበት ብሔር ሂዱ።”

 3 እናንተ በአገሪቱ የምትኖሩ ሁሉና እናንተ የምድር ነዋሪዎች ሁሉ፣

በተራሮች ላይ እንደሚቆም ምልክት* ያለ ነገር ትመለከታላችሁ፤

እንዲሁም ቀንደ መለከት ሲነፋ የሚሰማው ዓይነት ድምፅ ትሰማላችሁ።

 4 ይሖዋ እንዲህ ብሎኛልና፦

“በቀን ብርሃን እንዳለ የሚያጥበረብር ሐሩር፣

በመከርም ሙቀት እንዳለ የደመና ጠል፣

ጸጥ ብዬ ተቀምጬ ጽኑ ሆኖ የተመሠረተውን ስፍራዬን* እመለከታለሁ።

 5 ከመከር በፊት፣

አበባው በሚረግፍበትና የወይን ፍሬው በሚበስልበት ጊዜ

ቀንበጦቹ በማጭድ ይቆረጣሉና፤

ሐረጎቹም ተቆርጠው ይወገዳሉ።

 6 ሁሉም በተራሮች ላይ ላሉ አዳኝ አሞሮችና

ለምድር አራዊት ይተዋሉ።

አዳኝ አሞሮቹም እነሱን በመመገብ በጋውን ያሳልፋሉ፤

በምድር ላይ ያሉ አራዊትም ሁሉ እነሱን በመመገብ የመከሩን ወቅት ያሳልፋሉ።

 7 በዚያን ጊዜ ረጃጅም የሆኑና ለስላሳ ቆዳ ያላቸው ሰዎች የሚገኙበት ብሔር፣*

ከቅርብም ሆነ ከሩቅ የሚፈራው ሕዝብ፣

ጥንካሬ ያለው፣ ድል አድራጊ የሆነውና*

መሬቱ በወንዞች ተጠርጎ የተወሰደበት ብሔር

ለሠራዊት ጌታ ለይሖዋ ስጦታ ያመጣል፤

ስጦታውንም የሚያመጣው የሠራዊት ጌታ የይሖዋ ስም ወዳለበት ወደ ጽዮን ተራራ+ ነው።”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ