ኢሳይያስ
2 ይህች ምድር በባሕር ላይ፣
በደንገል ጀልባ ውኃዎችን አቋርጠው የሚሄዱ መልእክተኞችን እንዲህ በማለት ትልካለች፦
“እናንተ ፈጣን መልእክተኞች፣
ረጃጅም የሆኑና ለስላሳ ቆዳ ያላቸው ሰዎች ወደሚገኙበት ብሔር፣*
ከቅርብም ሆነ ከሩቅ ወደሚፈራ ሕዝብ፣+
ጥንካሬ ወዳለውና ድል አድራጊ ወደሆነው*
እንዲሁም መሬቱ በወንዞች ተጠርጎ ወደተወሰደበት ብሔር ሂዱ።”
3 እናንተ በአገሪቱ የምትኖሩ ሁሉና እናንተ የምድር ነዋሪዎች ሁሉ፣
በተራሮች ላይ እንደሚቆም ምልክት* ያለ ነገር ትመለከታላችሁ፤
እንዲሁም ቀንደ መለከት ሲነፋ የሚሰማው ዓይነት ድምፅ ትሰማላችሁ።
4 ይሖዋ እንዲህ ብሎኛልና፦
6 ሁሉም በተራሮች ላይ ላሉ አዳኝ አሞሮችና
ለምድር አራዊት ይተዋሉ።
አዳኝ አሞሮቹም እነሱን በመመገብ በጋውን ያሳልፋሉ፤
በምድር ላይ ያሉ አራዊትም ሁሉ እነሱን በመመገብ የመከሩን ወቅት ያሳልፋሉ።