የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • 1 ሳሙኤል 31
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

1 ሳሙኤል የመጽሐፉ ይዘት

      • ሳኦልና ሦስት ወንዶች ልጆቹ ሞቱ (1-13)

1 ሳሙኤል 31:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 14:52፤ 29:1
  • +1ሳሙ 28:4፤ 2ሳሙ 1:21፤ 1ዜና 10:1-5

1 ሳሙኤል 31:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 13:2
  • +1ዜና 8:33

1 ሳሙኤል 31:3

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 1:4, 6

1 ሳሙኤል 31:4

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እንዳይጫወቱብኝ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 17:26፤ 2ሳሙ 1:20
  • +1ዜና 10:4

1 ሳሙኤል 31:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 26:10፤ 1ዜና 10:13

1 ሳሙኤል 31:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 28:19፤ 1ዜና 10:6, 7

1 ሳሙኤል 31:7

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በረባዳማው ሜዳና።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 13:6

1 ሳሙኤል 31:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 28:4፤ 31:1፤ 2ሳሙ 1:6፤ 1ዜና 10:8-12

1 ሳሙኤል 31:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ቤተ መቅደሶችና።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መሳ 16:23
  • +2ሳሙ 1:20

1 ሳሙኤል 31:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 17:11፤ መሳ 1:27

1 ሳሙኤል 31:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 11:1, 9-11

1 ሳሙኤል 31:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ሳሙ 21:12
  • +2ሳሙ 2:4, 5

ተዛማጅ ሐሳብ

1 ሳሙ. 31:11ሳሙ 14:52፤ 29:1
1 ሳሙ. 31:11ሳሙ 28:4፤ 2ሳሙ 1:21፤ 1ዜና 10:1-5
1 ሳሙ. 31:21ሳሙ 13:2
1 ሳሙ. 31:21ዜና 8:33
1 ሳሙ. 31:32ሳሙ 1:4, 6
1 ሳሙ. 31:41ሳሙ 17:26፤ 2ሳሙ 1:20
1 ሳሙ. 31:41ዜና 10:4
1 ሳሙ. 31:51ሳሙ 26:10፤ 1ዜና 10:13
1 ሳሙ. 31:61ሳሙ 28:19፤ 1ዜና 10:6, 7
1 ሳሙ. 31:71ሳሙ 13:6
1 ሳሙ. 31:81ሳሙ 28:4፤ 31:1፤ 2ሳሙ 1:6፤ 1ዜና 10:8-12
1 ሳሙ. 31:9መሳ 16:23
1 ሳሙ. 31:92ሳሙ 1:20
1 ሳሙ. 31:10ኢያሱ 17:11፤ መሳ 1:27
1 ሳሙ. 31:111ሳሙ 11:1, 9-11
1 ሳሙ. 31:132ሳሙ 21:12
1 ሳሙ. 31:132ሳሙ 2:4, 5
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
1 ሳሙኤል 31:1-13

አንደኛ ሳሙኤል

31 ፍልስጤማውያን ከእስራኤል ጋር እየተዋጉ ነበር።+ የእስራኤልም ሰዎች ከፍልስጤማውያን ፊት ሸሹ፤ ብዙዎቹም በጊልቦአ+ ተራራ ላይ ተገደሉ። 2 ፍልስጤማውያንም ሳኦልንና ወንዶች ልጆቹን እግር በእግር ተከታተሏቸው፤ ፍልስጤማውያንም የሳኦልን ልጆች ዮናታንን፣+ አቢናዳብንና ሜልኪሳን መትተው ገደሏቸው።+ 3 ውጊያው በሳኦል ላይ በረታ፤ ቀስተኞቹም አገኙት፤ እነሱም ክፉኛ አቆሰሉት።+ 4 ከዚያም ሳኦል ጋሻ ጃግሬውን “እነዚህ ያልተገረዙ+ ሰዎች መጥተው እንዳይወጉኝና በጭካኔ እንዳያሠቃዩኝ* ሰይፍህን መዘህ ውጋኝ” አለው። ጋሻ ጃግሬው ግን እጅግ ፈርቶ ስለነበር ፈቃደኛ አልሆነም። በመሆኑም ሳኦል ሰይፉን ወስዶ በላዩ ላይ ወድቆ ሞተ።+ 5 ጋሻ ጃግሬውም ሳኦል መሞቱን ሲያይ+ እሱም በራሱ ሰይፍ ላይ ወድቆ ከእሱ ጋር ሞተ። 6 ስለዚህ ሳኦል፣ ሦስቱ ወንዶች ልጆቹ፣ ጋሻ ጃግሬውና የእሱ ሰዎች በሙሉ በዚያ ቀን አብረው ሞቱ።+ 7 በሸለቆውና* በዮርዳኖስ አካባቢ የነበሩት እስራኤላውያን፣ የእስራኤል ሠራዊት መሸሹን እንዲሁም ሳኦልና ልጆቹ መሞታቸውን ባዩ ጊዜ ከተሞቹን ጥለው ሸሹ፤+ ከዚያም ፍልስጤማውያን መጥተው ከተሞቹን ያዙ።

8 በማግስቱ ፍልስጤማውያን የሞቱትን ሰዎች ልብስና ትጥቅ ለመግፈፍ ሲመጡ ሳኦልንና ሦስቱን ወንዶች ልጆቹን በጊልቦአ+ ተራራ ላይ ወድቀው አገኟቸው። 9 ስለሆነም የሳኦልን ራስ ከቆረጡና የጦር ትጥቁን ከገፈፉ በኋላ ወሬው በጣዖቶቻቸው+ ቤቶችና* በሕዝቡ ሁሉ መካከል እንዲሰራጭ+ ለማድረግ በመላው የፍልስጤም ምድር መልእክት ላኩ። 10 ከዚያም የጦር ትጥቁን በአስታሮት ምስሎች ቤት አስቀመጡት፣ አስከሬኑን ደግሞ በቤትሻን+ ግንብ ላይ ቸነከሩት። 11 የኢያቢስጊልያድ+ ነዋሪዎችም ፍልስጤማውያን በሳኦል ላይ ያደረጉትን ሲሰሙ 12 ተዋጊዎቹ ሁሉ ተነስተው ሌሊቱን ሙሉ ሲጓዙ አደሩ፤ ከዚያም የሳኦልንና የልጆቹን አስከሬን ከቤትሻን ግንብ ላይ አወረዱ። ወደ ኢያቢስ ተመልሰውም በዚያ አቃጠሏቸው። 13 ከዚያም አፅማቸውን+ ወስደው በኢያቢስ+ በሚገኝ የታማሪስክ ዛፍ ሥር ቀበሩት፤ ለሰባት ቀንም ጾሙ።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ