የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • scl ገጽ 78-80
  • ኢየሱስ ክርስቶስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ኢየሱስ ክርስቶስ
  • ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
ጥቅሶች ለክርስቲያናዊ ሕይወት
scl ገጽ 78-80

ኢየሱስ ክርስቶስ

ኢየሱስ በይሖዋ ዓላማ አፈጻጸም ውስጥ ምን ወሳኝ ድርሻ አለው?

ሥራ 4:12፤ 10:43፤ 2ቆሮ 1:20፤ ፊልጵ 2:9, 10

በተጨማሪም ምሳሌ 8:22, 23, 30, 31፤ ዮሐ 1:10፤ ራእይ 3:14⁠ን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ማቴ 16:13-17—ሐዋርያው ጴጥሮስ፣ ስለ ኢየሱስ ማንነት ሲናገር ክርስቶስና የአምላክ ልጅ እንደሆነ ገልጿል

    • ማቴ 17:1-9—ኢየሱስ በሦስት ሐዋርያቱ ፊት በተአምራዊ ሁኔታ በተለወጠበት ወቅት ይሖዋ ከሰማይ ልጁ እንደሆነ ተናግሯል

ኢየሱስን ከሌሎች የሰው ልጆች ሁሉ የሚለየው ምንድን ነው?

ዮሐ 8:58፤ 14:9, 10፤ ቆላ 1:15-17፤ 1ጴጥ 2:22

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ማቴ 21:1-9—ኢየሱስ እንደ ድል አድራጊ ንጉሥ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ፣ በይሖዋ ስለተሾመው መሲሐዊ ንጉሥ የተነገረው ትንቢት ተፈጽሟል

    • ዕብ 7:26-28—ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ታላቁ ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ከሌሎቹ ሊቃነ ካህናት ሁሉ የሚለየው እንዴት እንደሆነ አብራርቷል

ኢየሱስ የፈጸማቸው ተአምራት ስለ እሱና ስለ አባቱ ምን ያስተምሩናል?

ዮሐ 3:1, 2፤ 5:36

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ማቴ 4:23, 24—ኢየሱስ በአጋንንት እንዲሁም በማንኛውም ዓይነት ሕመምና እክል ላይ ኃይል እንዳለው አሳይቷል

    • ማቴ 14:15-21—ኢየሱስ አምስት ዳቦና ሁለት ዓሣ ተጠቅሞ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በተአምር መግቧል

    • ማቴ 17:24-27—ኢየሱስ የይሖዋን አምልኮ ለመደገፍ እንዲሁም ሌሎችን ላለማሰናከል ሲል ለመዋጮ የሚሆን ገንዘብ በተአምር አስገኝቷል

    • ማር 1:40, 41—ኢየሱስ ለአንድ የሥጋ ደዌ ሕመምተኛ በጣም ስላዘነለት ፈወሰው፤ ይህም ሕመምተኞችን የሚፈውሰው ከልቡ ተነሳስቶ እንደሆነ ያሳያል

    • ማር 4:36-41—ኢየሱስ ኃይለኛ አውሎ ነፋስን ጸጥ አሰኝቷል፤ ይህም አባቱ በተፈጥሮ ኃይሎች ላይም እንኳ ሥልጣን እንደሰጠው ያሳያል

    • ዮሐ 11:11-15, 31-45—ኢየሱስ ወዳጁ አልዓዛር ሲሞት እንባውን አፍስሷል፤ ከዚያም አልዓዛርን ከሞት በማስነሳት ሞትንና በሰው ልጆች ላይ ያደረሰውን ሰቆቃ ምን ያህል እንደሚጠላ አሳይቷል

የኢየሱስ ትምህርት ዋነኛ ጭብጥ ምንድን ነው?

ማቴ 9:35፤ ሉቃስ 4:43፤ 8:1፤ ዮሐ 18:37

ኢየሱስ ምድር ሳለ የትኞቹን ማራኪ ባሕርያት አሳይቷል? እስቲ አንዳንዶቹን ተመልከት፦

ሩኅሩኅ፤ መሐሪ—ማር 5:25-34፤ ሉቃስ 7:11-15

በቀላሉ የሚቀረብ—ማቴ 13:2፤ ማር 10:13-16፤ ሉቃስ 7:36-50

ታዛዥ—ሉቃስ 2:40, 51, 52፤ ዕብ 5:8

ትሑት—ማቴ 11:29፤ 20:28፤ ዮሐ 13:1-5፤ ፊልጵ 2:7, 8

አፍቃሪ—ዮሐ 13:1፤ 14:31፤ 15:13፤ 1ዮሐ 3:16

ደፋር—ማቴ 4:2-11፤ ዮሐ 2:13-17፤ 18:1-6

ጥበበኛ—ማቴ 12:42፤ 13:54፤ ቆላ 2:3

ኢየሱስ ሕይወቱን መሥዋዕት አድርጎ የሰጠው ለምንድን ነው? ከዚህስ ምን ጥቅም እናገኛለን?

ማቴ 20:28፤ ዮሐ 3:16፤ ሥራ 10:43፤ 1ዮሐ 4:9, 10

ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማይ ንጉሥ ሆኖ እየገዛ መሆኑ የሚያስደስተን ለምንድን ነው?

መዝ 72:12-14፤ ዳን 2:44፤ 7:13, 14፤ ራእይ 12:9, 10

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • መዝ 45:2-7, 16, 17—ይህ መዝሙር አምላክ የመረጠው ንጉሥ ጠላቶቹን ሁሉ ድል እንደሚያደርግ እንዲሁም በእውነት፣ በትሕትናና በጽድቅ እንደሚገዛ ያሳያል

    • ኢሳ 11:1-10—ኢየሱስ ንጉሥ ሆኖ ምድርን ሲገዛ ምድር ሰላም የሰፈነባት ገነት ትሆናለች

ኢየሱስ በቅርቡ ምን ያደርጋል?

2ተሰ 1:7-9፤ 2:8፤ ራእይ 19:11-21

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ