የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w12 3/1 ገጽ 5
  • ‘የዓለም ክፍል አይደሉም’

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ‘የዓለም ክፍል አይደሉም’
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ክርስቲያኖችና ዛሬ ያለው ሰብአዊ ኅብረተሰብ
    መጠበቂያ ግንብ—1993
  • የይሖዋ ምሥክሮችና የሆሎኮስት ጥቃት—መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • ናዚዎች ያደረሱት እልቂት የተከሰተው ለምንድን ነው? አምላክ ጣልቃ ገብቶ ያላስቆመውስ ለምንድን ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • “ከዓለም አይደሉም”
    እውነተኛውን አንድ አምላክ አምልክ
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
w12 3/1 ገጽ 5

‘የዓለም ክፍል አይደሉም’

“የዓለም ክፍል ስላልሆኑ ዓለም ጠላቸው።”​—ዮሐንስ 17:14

ይህ ምን ማለት ነው? ኢየሱስ የዓለም ክፍል ስላልነበር በዘመኑ በነበሩት ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ግጭቶች ረገድ ገለልተኛ ነበር። “መንግሥቴ የዚህ ዓለም ክፍል ቢሆን ኖሮ በአይሁዳውያን እጅ እንዳልወድቅ አገልጋዮቼ ይዋጉልኝ ነበር። አሁን ግን መንግሥቴ ከዚህ አይደለም” በማለት ተናግሯል። (ዮሐንስ 18:36) ተከታዮቹንም የአምላክ ቃል ከሚያወግዘው ዝንባሌ፣ ንግግርና ምግባር እንዲርቁ አሳስቧቸዋል።​—ማቴዎስ 20:25-27

የጥንቶቹ ክርስቲያኖች ይህን ብቃት አሟልተዋል? ስለ ሃይማኖታዊ ጉዳዮች የሚጽፉት ጆናታን ዳይመንድ እንደተናገሩት የጥንቶቹ ክርስቲያኖች “መዘዙ ምንም ይሁን ምን፣ ውርደትና እስራት ወይም ሞት ቢያስከትልባቸው እንኳ [በጦርነት] አይካፈሉም ነበር።” እነዚያ ክርስቲያኖች የገለልተኝነት አቋማቸውን ከማላላት ይልቅ መሠቃየትን ይመርጡ ነበር። የሚከተሉት የሥነ ምግባር ደንብም ቢሆን ከሌሎች የተለዩ ያደርጋቸው ነበር። ክርስቲያኖች “ይህን በመሰለው ያዘቀጠ ወራዳ ሕይወት ከእነሱ ጋር መሮጣችሁን ስለማትቀጥሉ ይደነቃሉ እንዲሁም ይሰድቧችኋል” ተብለዋል። (1 ጴጥሮስ 4:4) የታሪክ ምሁር የሆኑት ዊል ዱራንት፣ የክርስቲያኖች ማኅበረሰብ “ተድላ ያሳበደውን አረማዊ ዓለም በመንፈሳዊ አቋሙና በመልካም ምግባሩ ይኮንነው ነበር” በማለት ጽፈዋል።

በዛሬው ጊዜ ብቃቱን የሚያሟሉት እነማን ናቸው? ክርስቲያናዊ ገለልተኝነትን በተመለከተ ኒው ካቶሊክ ኢንሳይክሎፒድያ እንዲህ ይላል፦ “በሕሊና ምክንያት በጦርነት አለመካፈል ከሥነ ምግባር አንጻር ተቀባይነት የለውም።” የ1994ቱን የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ዘመቻ አስመልክቶ አንድ የአፍሪካ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ያወጣው ዘገባ “ከይሖዋ ምሥክሮች በስተቀር” ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት በዚህ ጭፍጨፋ መካፈላቸውን እንዳረጋገጠ ሬፎርሚርቴ ፕሬሴ ላይ የወጣ ርዕስ ይገልጻል።

አንድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር ናዚዎች ያደረሱትን እልቂት አስመልክቶ እንዲህ በማለት በምሬት ተናግሯል፦ “ያን ሁሉ ውሸትና ጭካኔ እንዲሁም ውሎ አድሮ የተከተለውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ በድፍረት የተቃወመ . . . አንድም ቡድን ወይም ድርጅት አልነበረም።” ይህ አስተማሪ በዩናይትድ ስቴትስ የሚገኘውን የናዚ እልቂት ሰለባዎች ቤተ መዘክር ከጎበኘ በኋላ ግን “አሁን መልሱን አግኝቻለሁ” በማለት ጽፏል። መምህሩ፣ የይሖዋ ምሥክሮች ከባድ ሥቃይ ቢደርስባቸውም በእምነታቸው ጸንተው እንደቆሙ ማወቅ ችሏል።

የይሖዋ ምሥክሮች ስለሚከተሉት የሥነ ምግባር ደንብስ ምን ማለት ይቻላል? “በዛሬው ጊዜ ካሉት ወጣት ካቶሊኮች መካከል አብዛኞቹ፣ ከጋብቻ በፊት አብሮ መኖርን [እና] ሳይጋቡ በፊት የፆታ ግንኙነት መፈጸምን በመሳሰሉት ጉዳዮች ረገድ ቤተ ክርስቲያኗ የምታስተምረውን ትምህርት አይቀበሉም” በማለት ዩ ኤስ ካቶሊክ የተሰኘው መጽሔት ይናገራል። አንድ የቤተ ክርስቲያን ዲያቆን “አብዛኞቹ ተጋቢዎች፣ ምናልባትም ከ50 በመቶ በላይ የሚሆኑት አብረው ሲኖሩ የቆዩ ናቸው” በማለት እንደተናገረ መጽሔቱ ይጠቅሳል። በሌላ በኩል ግን ዘ ኒው ኢንሳይክሎፒድያ ብሪታኒካ እንደገለጸው የይሖዋ ምሥክሮች “በአኗኗራቸው ከፍተኛ የሥነ ምግባር ደንቦችን መከተል እንዳለባቸው ያምናሉ።”

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ