ማስታወቂያዎች
◼ የሚበረከቱ ጽሑፎች የካቲት:- ወደ ይሖዋ ቅረብ፤ መጋቢት:- ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው? ሚያዝያና ግንቦት:- መጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! መጽሔቶች። ተመላልሶ መጠየቅ በምታደርጉበት ወቅት ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው? የተባለውን መጽሐፍ አበርክቱ።
◼ ጸሐፊውና የአገልግሎት የበላይ ተመልካቹ የሁሉንም የዘወትር አቅኚዎች የአገልግሎት እንቅስቃሴ መመርመር ይኖርባቸዋል። የሰዓት ግባቸው ላይ መድረስ ያልቻሉ አቅኚዎች ካሉ ሽማግሌዎቹ እርዳታ መስጠት የሚቻልበትን መንገድ መቀየስ ይኖርባቸዋል። ተጨማሪ ሐሳብ ለማግኘት ዓመታዊ S-201 ደብዳቤዎችን ተመልከቱ።
◼ በመታሰቢያው በዓል ሰሞን የሚቀርበው የ2007 ልዩ የሕዝብ ንግግር ርዕስ “በመከራ በተሞላው በዚህ ዓለም ውስጥ ያለ ስጋት መኖር ትችላለህ!” የሚል ይሆናል። ከዚህ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ሌሎች ጉዳዮች በሚመለከት በጥቅምት 2006 የመንግሥት አገልግሎታችን ላይ የወጣውን ማስታወቂያ ተመልከቱ።
◼ አዲስ የደረሱን ጽሑፎች:- ቀለል ባለ ቻይንኛ:- አምላክ ከእኛ የሚፈልገው፣ ትራክት ቁ. 26 (ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ይበልጥ ማወቅ ትፈልጋለህ?)፤ እንግሊዝኛ:- የመንግሥቱ ጣዕመ ዜማዎች ቁ. 4 በሲዲ፣ ኖኅና ዳዊት የተባለው ዲቪዲ፣ የወጣቶች ጥያቄ—ሕይወቴን እንዴት ብጠቀምበት ይሻላል? በዲቪዲ፣ ጅሆቫስ ዊትነስስ—ኦርጋናይዝድ ቱ ሼር ዘ ጉድ ኒውስ በዲቪዲ፤ ትግርኛ:- የውይይት አርዕስት።
◼ በድጋሚ የደረሱን ጽሑፎች:- እንግሊዝኛ:- አምላክ ከእኛ የሚፈልገው፤ ኦሮምኛ:- የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት፣ ነቅተህ ጠብቅ!፣ አምላክ ከእኛ የሚፈልገው፣ ትራክት ቁ. 15 (ሰላም በሰፈነበት አዲስ ዓለም ውስጥ የሚገኝ ሕይወት)፤ ትግርኛ:- የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት፣ ትራክት ቁ. 19 (ይህ ዓለም ከጥፋት ይተርፍ ይሆን?) እና ቁ. 20 (ለተጨነቁ ሰዎች የሚሆን መጽናኛ)።