የመስክ አገልግሎት ጎላ ያሉ ገጽታዎች
በአገራችን 8,851 የደረሰ አዲስ ከፍተኛ የአስፋፊዎች ቁጥር በማግኘታችን ሁላችንም ተደስተናል! ከእነዚህ መካከል 1,001 የሚሆኑት ረዳት አቅኚዎች ነበሩ። አብዛኞቻችሁ ረዳት አቅኚ በመሆን አገልግሎታችሁን ማስፋት የቻላችሁት የትምህርት ቤት የእረፍት ጊዜያችሁን ተጠቅማችሁ ነው፤ ይህ ደግሞ ደስታ እንዳስገኘላችሁ እንተማመናለን። ከመታሰቢያው በዓል በኋላም ብዙዎች መሥዋዕትነት ከፍለው ረዳት አቅኚ በመሆን የአገልግሎት እንቅስቃሴያቸውን በማስፋታቸው ተደስተናል። በነሐሴ ወርም አንዳንዶች ረዳት አቅኚ እንደሚሆኑ ተስፋ እናደርጋለን፤ የነሐሴን ሪፖርት ለማየት በጉጉት እንጠባበቃለን። የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶቻችን ቁጥር ጨምሮ በሐምሌ ወር 7,030 መድረሱን ስትሰሙ እንደምትደሰቱ ጥርጥር የለውም። ፍላጎት ያላቸውን ሰዎች ተከታትለን በመርዳት ለሌሎች ያለንን ፍቅር እንድንገልጽ አንዳችን ሌላውን እናስታውስ፤ እንዲሁም በዚህ ረገድ እርስ በርስ እንበረታታ። በተጨማሪም ከጥናቶቻችን መካከል አንዳንዶቹ ያልተጠመቁ አስፋፊዎች ለመሆን ብቃቱን ያሟሉ ይሆን?