ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት | ሮም 9-11
የወይራ ዛፉ ምሳሌ
የምሳሌያዊው የወይራ ዛፍ የተለያዩ ክፍሎች ምን ያመለክታሉ?
ዛፉ፦ አምላክ ከአብርሃም ቃል ኪዳን ጋር በተያያዘ ያለውን ዓላማ አፈጻጸም
ግንዱ፦ የአብርሃም ዘር ዋነኛ ክፍል የሆነውን ኢየሱስን
ቅርንጫፎቹ፦ በአብርሃም ዘር ሁለተኛ ክፍል ውስጥ የሚካተቱትን ሰዎች ሙሉ ቁጥር
“የተሰበሩት” ቅርንጫፎች፦ ኢየሱስን ያልተቀበሉትን ሥጋዊ እስራኤላውያን
‘የተጣበቁት’ ቅርንጫፎች፦ ከአሕዛብ ወገን የሆኑትን ቅቡዓን ክርስቲያኖች
በትንቢት እንደተነገረው የአብርሃም ዘር ማለትም ኢየሱስና 144,000ዎቹ “ለአሕዛብ በረከት” ያስገኛሉ።—ሮም 11:12፤ ዘፍ 22:18
ይሖዋ ከአብርሃም ዘር ጋር በተያያዘ ያለውን ዓላማ የፈጸመበት መንገድ ስለ እሱ ምን ያስተምረኛል?