የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 15
  • የሎጥ ሚስት ወደ ኋላ ተመለከተች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የሎጥ ሚስት ወደ ኋላ ተመለከተች
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የሎጥን ሚስት አስታውሱ
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • አምላክ ከአብርሃም ጋር ቃል ኪዳን ገባ
    መጽሐፍ ቅዱስ—የያዘው መልእክት ምንድን ነው?
  • ሎጥ እና ቤተሰቡ
    ሥዕላዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች
  • የሚያስጨንቁ ሁኔታዎች ያጋጠሟቸውን እርዷቸው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2019
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 15

ምዕራፍ 15

የሎጥ ሚስት ወደ ኋላ ተመለከተች

ሎጥና ቤተሰቡ ከአብርሃም ጋር በከነዓን ምድር ይኖሩ ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን አብርሃም ሎጥን ‘በዚህ ቦታ ለእንስሶቻችን በሙሉ የሚበቃ መሬት የለም። እባክህን እንለያይ። አንተ በዚህ ብትሄድ እኔ በዚያ እሄዳለሁ’ አለው።

ሎጥ ምድሪቱን በደንብ ተመለከተ። ውኃ ያለበትንና ለእንስሳቱ የሚሆን ብዙ ጥሩ ሣር የሚገኝበትን በጣም የሚያምር አካባቢ አየ። ይህ በዮርዳኖስ ክልል ውስጥ የሚገኝ ቦታ ነበር። ስለዚህ ሎጥ ቤተሰቡንና እንስሶቹን ይዞ ወደዚያ ሄደ። በመጨረሻም በሰዶም ከተማ ውስጥ መኖር ጀመሩ።

የሰዶም ሰዎች በጣም መጥፎዎች ነበሩ። ሎጥ ጥሩ ሰው ስለ ነበር ይህ ሁኔታ አበሳጭቶት ነበር። አምላክም ቢሆን ተቆጥቶ ነበር። በመጨረሻ አምላክ ሰዎቹ መጥፎዎች በመሆናቸው የተነሳ ሰዶምንና በአቅራቢያው የነበረችውን ጎሞራ የተባለች ከተማ ሊያጠፋቸው መሆኑን ለሎጥ እንዲነግሩ ሁለት መላእክት ላከ።

መላእክቱ ሎጥን ‘ቶሎ በል! ሚስትህንና ሁለቱን ሴቶች ልጆችህን ይዘህ ከዚህ ከተማ ውጣ!’ አሉት። ሎጥና ቤተሰቡ ትንሽ ስለ ዘገዩ መላእክቱ እጃቸውን ይዘው ከከተማው አስወጧቸው። ከዚያም ከመላእክቱ አንዱ ‘ሕይወታችሁን አድኑ! ወደ ኋላ አትመልከቱ። እንዳትሞቱ ወደ ተራሮቹ ሽሹ’ አላቸው።

ሎጥና ሴቶች ልጆቹ የታዘዙትን በማድረግ ከሰዶም ሸሹ። ለጥቂት ጊዜም እንኳ ቆም አላሉም፤ ወደ ኋላም አልተመለከቱም። የሎጥ ሚስት ግን የተሰጠውን ትእዛዝ ጣሰች። ከሰዶም ወጥተው ጥቂት ከተጓዙ በኋላ ቆመችና ወደ ኋላ ተመለከተች። ከዚያም የሎጥ ሚስት የጨው ሐውልት ሆነች። ሥዕሉ ላይ አየሃት?

ከዚህ ጥሩ ትምህርት ማግኘት እንችላለን። አምላክ የሚታዘዙትን እንደሚያድንና እርሱን የማይታዘዙ ግን ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ያሳያል።

ዘፍጥረት 13:​5-13፤ 18:​20-33፤ 19:​1-29፤ ሉቃስ 17:​28-32፤ 2 ጴጥሮስ 2:​6-8

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ