የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • my ታሪክ 29
  • ሙሴ የሸሸበት ምክንያት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ሙሴ የሸሸበት ምክንያት
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በእሳት የተያያዘው ቁጥቋጦ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • በእሳት የተያያዘው ቁጥቋጦ
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • የይሖዋን መንገድ መማር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
  • እምነት በማሳየት ረገድ ሙሴን ምሰሉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2014
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
my ታሪክ 29

ምዕራፍ 29

ሙሴ የሸሸበት ምክንያት

ሙሴ ከግብፅ ሲሸሽ ተመልከት። እያሳደዱት ያሉትን ሰዎች አየሃቸው? ሙሴን ለመግደል የፈለጉበትን ምክንያት ታውቃለህ? እስቲ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ለማወቅ እንመርምር።

ሙሴ በግብፅ ገዥ በፈርዖን ቤት ውስጥ አደገ። በጣም ጥበበኛና ታላቅ ሰው ሆነ። ሙሴ ግብፃዊ አለመሆኑን ከዚህ ይልቅ የወለዱት ወላጆቹ እስራኤላውያን ባሪያዎች መሆናቸውን ያውቅ ነበር።

ከዕለታት አንድ ቀን ሙሴ 40 ዓመት ሲሞላው ወገኖቹ በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ ሄዶ ለመመልከት ወሰነ። በጣም አስከፊ የሆነ ድርጊት ይፈጸምባቸው ነበር። አንድ ግብፃዊ አንድን እስራኤላዊ ባሪያ ሲመታው ተመለከተ። ሙሴ ዙሪያውን ተመለከተና ማንም የሚያየው እንደሌለ ሲያውቅ ግብፃዊውን መታውና ገደለው። ከዚያም ሙሴ ሰውዬውን አሸዋ ውስጥ ደበቀው።

በሚቀጥለው ቀን ሙሴ እንደገና ወገኖቹን ለመመልከት ሄደ። ከባርነት ነፃ እንዲወጡ ልረዳቸው እችላለሁ ብሎ አስቦ ነበር። ይሁን እንጂ ሁለት እስራኤላውያን ሲጣሉ ተመለከተና ጥፋተኛውን ሰውዬ ‘ወንድምህን ለምን ትመታዋለህ?’ አለው።

ሰውዬው ‘አንተን በእኛ ላይ አለቃና ዳኛ ያደረገህ ማን ነው? ያንን ግብፃዊ እንደገደልከው እኔንም ልትገድለኝ ነው?’ አለው።

በዚህ ጊዜ ሙሴ በጣም ፈራ። በግብፃዊው ላይ የፈጸመውን ነገር ሰዎች እንዳወቁት ተገነዘበ። ፈርዖንም ሙሴ የፈጸመውን ነገር ሰማና እንዲገድሉት ሰዎችን ላከ። ሙሴ ከግብፅ የሸሸው በዚህ ምክንያት ነው።

ሙሴ ከግብፅ ከወጣ በኋላ ከዚያ ርቆ ወደሚገኘው ወደ ምድያም ምድር ተጓዘ። በዚያ ስፍራም ከዮቶር ቤተሰብ ጋር ተገናኘና ሲፓራ የተባለችውን የዮቶር ልጅ አገባ። ሙሴ እረኛ ሆነና የዮቶርን በጎች ይጠብቅ ጀመር። በምድያም ምድር 40 ዓመት ኖረ። አሁን 80 ዓመት ሆኖታል። ከዕለታት አንድ ቀን ሙሴ የዮቶርን በጎች እየጠበቀ ሳለ መላውን የሙሴ ሕይወት የለወጠ አንድ አስገራሚ ነገር ተፈጸመ። ገጹን ግለጥና ይህ አስገራሚ ነገር ምን እንደሆነ እንመልከት።

ዘጸአት 2:​11-25፤ ሥራ 7:​22-29

የአንቀጾቹ ጥያቄዎች

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ