የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • jl ትምህርት 12
  • የመንግሥቱን ምሥራች የምንሰብከው እንዴት ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የመንግሥቱን ምሥራች የምንሰብከው እንዴት ነው?
  • በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የይሖዋ ምሥክሮች ከቤት ወደ ቤት የሚሰብኩት ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
  • ምሥራቹ እየተሰበከ ያለው እንዴት ነው?
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
  • “ሂዱና ከሁሉም ብሔራት ሰዎችን ደቀ መዛሙርት አድርጉ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • ስለ አምላክ መንግሥት ለመስበክ የተደራጁ ጉባኤዎች
    እንደ አንድ አካል ሆነው በዓለም ዙሪያ የአምላክን ፈቃድ የሚያደርጉት የይሖዋ ምሥክሮች
ለተጨማሪ መረጃ
በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
jl ትምህርት 12

ትምህርት 12

የመንግሥቱን ምሥራች የምንሰብከው እንዴት ነው?

የይሖዋ ምሥክሮች ከቤት ወደ ቤት እየሄዱ ሲሰብኩ

ስፔን

አንድ የይሖዋ ምሥክር መናፈሻ ውስጥ ሲሰብክ

ቤላሩስ

አንዲት የይሖዋ ምሥክር በስልክ ስትሰብክ

ሆንግ ኮንግ

በስብከት ሥራቸው ላይ ያሉ የይሖዋ ምሥክሮች

ፔሩ

ኢየሱስ ከመሞቱ ጥቂት ቀደም ብሎ “ይህ የመንግሥቱ ምሥራች ለብሔራት ሁሉ ምሥክር እንዲሆን በመላው ምድር ይሰበካል፤ ከዚያም መጨረሻው ይመጣል” በማለት ተናግሮ ነበር። (ማቴዎስ 24:14) ይሁን እንጂ ይህ ዓለም አቀፍ የስብከት ሥራ የሚከናወነው እንዴት ነው? ኢየሱስ ምድር ሳለ የተወውን ምሳሌ በመከተል ነው።—ሉቃስ 8:1

ሰዎችን ቤታቸው ሄደን ለማነጋገር ጥረት እናደርጋለን። ኢየሱስ ምሥራቹን ከቤት ወደ ቤት እየሄዱ እንዲሰብኩ ደቀ መዛሙርቱን አሠልጥኗቸው ነበር። (ማቴዎስ 10:11-13፤ የሐዋርያት ሥራ 5:42፤ 20:20) በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበሩት እነዚህ ወንጌላውያን የሚሰብኩበት ክልል ተመድቦላቸው ነበር። (ማቴዎስ 10:5, 6፤ 2 ቆሮንቶስ 10:13) ዛሬም በተመሳሳይ የስብከት ሥራችን በሚገባ የተደራጀ ሲሆን እያንዳንዱ ጉባኤም ሊሸፍነው የሚገባ የራሱ ክልል ተመድቦለታል። ይህም “ለሰዎች እንድንሰብክና በተሟላ ሁኔታ እንድንመሠክር” የሚያዝዘውን የኢየሱስን መመሪያ ለመፈጸም ያስችለናል።—የሐዋርያት ሥራ 10:42

ሰዎች በሚገኙበት ቦታ ሁሉ ለመስበክ ጥረት እናደርጋለን። ኢየሱስ ብዙ ሕዝብ በሚገኝባቸው ቦታዎችም ለምሳሌ በባሕር ዳርቻዎችና በውኃ ጉድጓዶች አቅራቢያ በመስበክ አርዓያ ትቶልናል። (ማርቆስ 4:1፤ ዮሐንስ 4:5-15) እኛም ሰዎችን ማግኘት በምንችልበት ቦታ ሁሉ ይኸውም በመንገድ ላይ፣ በንግድ አካባቢዎችና በመናፈሻ ቦታዎች አሊያም ደግሞ በስልክ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ እናወያያቸዋለን። በተጨማሪም አመቺ አጋጣሚ በምናገኝበት ጊዜ ለጎረቤቶቻችን፣ ለሥራ ባልደረቦቻችን፣ አብረውን ለሚማሩ ልጆችና ለዘመዶቻችን ሁሉ እንመሠክራለን። ምሥራቹን ለመስበክ የምናደርገው ይህ ሁሉ ጥረት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች “የማዳኑን ምሥራች” እንዲሰሙ አስችሏል።—መዝሙር 96:2

ስለ አምላክ መንግሥትና ወደፊት ስለሚያመጣቸው ነገሮች የሚገልጸውን ምሥራች ልትነግረው የምትፈልገው ሰው አለ? ይህን አስደሳች ተስፋ ሚስጥር አድርገህ አትያዘው። ዛሬ ነገ ሳትል ይህን ምሥራች ለሌሎች ተናገር!

  • መሰበክ ያለበት “ምሥራች” የትኛው ነው?

  • የይሖዋ ምሥክሮች፣ ኢየሱስ ምሥራቹን የሰበከበትን መንገድ የሚኮርጁት እንዴት ነው?

ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት

ከመጽሐፍ ቅዱስ የተማርከውን ነገር ለአንድ የምታውቀው ሰው እንዴት በዘዴ መናገር እንደምትችል የመጽሐፍ ቅዱስ አስጠኚህ እንዲያሳይህ ጠይቀው።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ