የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • jy ምዕ. 29 ገጽ 72-ገጽ 73 አን. 8
  • በሰንበት መልካም ሥራ መሥራት ይፈቀዳል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • በሰንበት መልካም ሥራ መሥራት ይፈቀዳል?
  • ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በሰንበት መልካም ሥራ መሥራት
    እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው
  • የሰው ልጆችን ይወዳል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • “ሄደህ በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠብ”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2007
  • ኢየሱስ የታመሙ ሰዎችን ፈወሰ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
ለተጨማሪ መረጃ
ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
jy ምዕ. 29 ገጽ 72-ገጽ 73 አን. 8
ኢየሱስ አንድን የታመመ ሰው በቤተዛታ ገንዳ አጠገብ ሲያናግረው

ምዕራፍ 29

በሰንበት መልካም ሥራ መሥራት ይፈቀዳል?

ዮሐንስ 5:1-16

  • ኢየሱስ በይሁዳ ሰበከ

  • በውኃ ገንዳ አጠገብ ያገኘውን የታመመ ሰው ፈወሰ

ኢየሱስ በገሊላ ባከናወነው ታላቅ አገልግሎት ብዙ ነገሮችን አድርጓል። ይሁንና “ለሌሎች ከተሞችም የአምላክን መንግሥት ምሥራች ማወጅ አለብኝ” ሲል በገሊላ ብቻ ስለ መስበክ መናገሩ አልነበረም። በመሆኑም “በይሁዳ ምኩራቦች መስበኩን ቀጠለ።” (ሉቃስ 4:43, 44) ጊዜው ጸደይ ስለሆነና በኢየሩሳሌም የሚከበረው በዓል እየተቃረበ ስለመጣ በዚህ ወቅት ኢየሱስ በይሁዳ መስበኩ ተገቢ ነው።

ኢየሱስ በገሊላ ስላከናወነው አገልግሎት ከሚገልጹት ዘገባዎች አንጻር ሲታይ በይሁዳ ስለፈጸማቸው ነገሮች በወንጌሎች ውስጥ ተመዝግቦ የምናገኘው ሐሳብ አነስተኛ ነው። በይሁዳ አብዛኛው ሕዝብ ግዴለሽ ቢሆንም ይህ ኢየሱስ በቅንዓት ከመስበክና በሄደበት ቦታ ሁሉ መልካም ነገር ከማድረግ ወደኋላ እንዲል አላደረገውም።

ብዙም ሳይቆይ ኢየሱስ በ31 ዓ.ም. በሚከበረው የፋሲካ በዓል ላይ ለመገኘት የይሁዳ ዋና ከተማ ወደሆነችው ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘ። ሰው በሚበዛበት በበጎች በር አጠገብ ቤተዛታ ተብሎ የሚጠራ በዙሪያው መተላለፊያዎች ያሉት ትልቅ የውኃ ገንዳ አለ። በርካታ ሕመምተኞች፣ ዓይነ ስውሮችና አንካሶች ወደዚህ ገንዳ ይመጣሉ። ለምን? ብዙዎች፣ ውኃው በሚናወጥበት ጊዜ ገንዳው ውስጥ መግባት ፈውስ እንደሚያስገኝ ስለሚያምኑ ነው።

ዕለቱ ሰንበት ነው፤ ኢየሱስ ለ38 ዓመታት ታሞ የቆየ አንድ ሰው በገንዳው አጠገብ አየ። በመሆኑም ይህን ሰው “መዳን ትፈልጋለህ?” ሲል ጠየቀው። ሰውየውም እንዲህ ሲል መለሰለት፦ “ጌታዬ፣ ውኃው በሚናወጥበት ጊዜ ገንዳው ውስጥ የሚያስገባኝ ሰው የለኝም፤ ወደ ገንዳው ስሄድ ደግሞ ሌላው ቀድሞኝ ይገባል።”—ዮሐንስ 5:6, 7

በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ሰውየውንም ሆነ በአቅራቢያው ሆነው የሚሰሙ ሰዎችን የሚያስደንቅ ነገር ተናገረ፤ “ተነስ! መኝታህን ተሸክመህ ሂድ” አለው። (ዮሐንስ 5:8 ግርጌ) ሰውየውም ያደረገው ይህንኑ ነው። ወዲያው ስለተፈወሰ መኝታውን ይዞ ሄደ!

አይሁዳውያን ኢየሱስ የፈወሰውን ሰው ሲያናግሩት

አይሁዳውያን በዚህ አስደናቂ ተአምር ከመደሰት ይልቅ ሰውየውን ሲያዩ “ሰንበት እኮ ነው፤ መኝታህን እንድትሸከም ሕጉ አይፈቅድልህም” ብለው ኮነኑት። ሰውየውም “የፈወሰኝ ሰው ራሱ ‘መኝታህን ተሸክመህ ሂድ’ ብሎኛል” ሲል መለሰላቸው። (ዮሐንስ 5:10, 11 ግርጌ) እነዚህ አይሁዳውያን በሰንበት የሚፈውስ ሰው መኖሩ አላስደሰታቸውም።

ስለዚህ “‘መኝታህን ተሸክመህ ሂድ’ ያለህ ሰው ማን ነው?” ሲሉ ጠየቁት። ሰውየውን እንዲህ ብለው የጠየቁት ለምንድን ነው? “ኢየሱስ ከቦታው ዞር ብሎ ከሕዝቡ ጋር ተቀላቅሎ ስለነበር” ነው፤ ሰውየው ደግሞ የኢየሱስን ስም አያውቀውም። (ዮሐንስ 5:12, 13 ግርጌ) ይሁን እንጂ ሰውየውና ኢየሱስ እንደገና ሊገናኙ ነው። በኋላ ላይ በቤተ መቅደሱ ውስጥ ይህ ሰው ኢየሱስን ሲያገኘው በገንዳው አጠገብ የፈወሰው ማን እንደሆነ አወቀ።

የተፈወሰው ሰው፣ ማን እንዳዳነው ከጠየቁት አይሁዳውያን ጋር ሲገናኝ የፈወሰው ኢየሱስ መሆኑን ነገራቸው። አይሁዳውያኑ ይህን ሲሰሙ ወደ ኢየሱስ ሄዱ። ወደ እሱ የሄዱት እነዚህን ተአምራት መፈጸም የቻለው እንዴት እንደሆነ ለማወቅ ፈልገው ይሆን? አይደለም። ከዚህ ይልቅ በሰንበት መልካም ነገሮች በመሥራቱ እሱን ለመንቀፍ ነው። እንዲያውም ስደት ያደርሱበት ጀመር!

  • ኢየሱስ ወደ ይሁዳ የሄደው ለምንድን ነው? ምን ማድረጉንስ አላቆመም?

  • ቤተዛታ ወደተባለው ገንዳ ብዙዎች የሚሄዱት ለምንድን ነው?

  • ኢየሱስ በገንዳው አጠገብ ምን ተአምር ፈጸመ? አንዳንድ አይሁዳውያን ይህን ሲያዩ ምን አደረጉ?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ