የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 30 ገጽ 76
  • ረዓብ ሰላዮቹን ደበቀች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ረዓብ ሰላዮቹን ደበቀች
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ረዓብ በይሖዋ ላይ እምነት ነበራት
    ልጆቻችሁን አስተምሩ
  • ረዓብ ዜናውን ሰምታ ነበር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
  • ረዓብ ሰላዮቹን ደበቀች
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ረዓብ “በሥራ ጻድቅ ተብላ” ተጠርታለች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 30 ገጽ 76
ረዓብ ወታደሮቹን ወደ ሌላ አቅጣጫ በመላክ ሰላዮቹን አዳነቻቸው

ትምህርት 30

ረዓብ ሰላዮቹን ደበቀች

ኢያሱ የላካቸው ሰላዮች ወደ ኢያሪኮ ሄደው ረዓብ ወደምትባል ሴት ቤት ገቡ። የኢያሪኮ ንጉሥ፣ ሰላዮች መምጣታቸውን ስለሰማ ወደ ረዓብ ቤት ወታደሮችን ላከ። ረዓብ ሁለቱን ሰላዮች ጣሪያ ላይ ደበቀቻቸውና ወታደሮቹን በሌላ አቅጣጫ ላከቻቸው። ከዚያም ሰላዮቹን እንዲህ አለቻቸው፦ ‘ይሖዋ ከእናንተ ጋር እንደሆነና ምድሪቱን እንደሚሰጣችሁ ስለማውቅ እረዳችኋለሁ። እባካችሁ ቤተሰቤን እንደምታድኑልኝ ቃል ግቡልኝ።’

ሰላዮቹ ረዓብን እንዲህ አሏት፦ ‘በቤትሽ ያለ ማንኛውም ሰው ፈጽሞ ጉዳት እንደማይደርስበት ቃል እንገባልሻለን። መስኮትሽ ላይ ቀይ ገመድ አንጠልጥይ፤ እንዲህ ካደረግሽ ቤተሰብሽ ይድናል።’

የኢያሪኮ አጥር ሲፈርስ መስኮቱ ላይ ቀይ ገመድ የተንጠለጠለበት የረዓብ ቤት አልፈረሰም

ረዓብ ሰላዮቹን በመስኮት በኩል በገመድ አወረደቻቸው። እነሱም ወደ ተራሮች ሄደው ለሦስት ቀን ከተደበቁ በኋላ ወደ ኢያሱ ተመልሰው ሄዱ። ከዚያም እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ወንዝ በመሻገር ከተማዋን ለመያዝ ተዘጋጁ። እስራኤላውያን ድል ካደረጓቸው ከተሞች የመጀመሪያዋ ኢያሪኮ ነበረች። ይሖዋ ለስድስት ቀናት ያህል በቀን አንዴ ከተማዋን እንዲዞሯት ነገራቸው። በሰባተኛው ቀን ግን ከተማዋን ሰባት ጊዜ ዞሯት። ከዚያም ካህናቱ ቀንደ መለከታቸውን ነፉ፤ ወታደሮቹ ደግሞ ባለ በሌለ ኃይላቸው ጮኹ። በዚህ ጊዜ የከተማዋ አጥር ፈራረሰ! ከአጥሩ ጋር ተያይዞ የተሠራው የረዓብ ቤት ግን አልፈረሰም። ረዓብ በይሖዋ ስለታመነች እሷም ሆነች ቤተሰቧ መትረፍ ችለዋል።

“ረዓብም መልእክተኞቹን በጥሩ ሁኔታ ተቀብላ ካስተናገደቻቸውና በሌላ መንገድ ከላከቻቸው በኋላ በሥራ አልጸደቀችም?”—ያዕቆብ 2:25

ጥያቄ፦ ረዓብ ሰላዮቹን የረዳቻቸው ለምንድን ነው? እስራኤላውያን በኢያሪኮ ላይ ጥቃት የሰነዘሩት እንዴት ነው? ረዓብና ቤተሰቧ ምን ሆኑ?

ኢያሱ 2:1-24፤ 6:1-27፤ ዕብራውያን 11:30, 31፤ ያዕቆብ 2:24-26

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ