የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 35 ገጽ 86
  • ሐና ልጅ ለማግኘት ጸለየች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ሐና ልጅ ለማግኘት ጸለየች
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ለአምላክ የልቧን አውጥታ ነገረችው
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
  • ለአምላክ የልቧን አውጥታ ነገረችው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2010
  • ሐና ሰላም ያገኘችው እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2007
  • ይሖዋ የሚያረጋጋን እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 35 ገጽ 86
ሐና ሕፃኑን ሳሙኤልን ወደ ቤተ መቅደሱ ወስዳ ለኤሊ ስትሰጠው

ትምህርት 35

ሐና ልጅ ለማግኘት ጸለየች

ሕልቃና የሚባል አንድ እስራኤላዊ ሐና እና ፍናና የተባሉ ሁለት ሚስቶች ነበሩት፤ ሆኖም ሕልቃና አስበልጦ የሚወደው ሐናን ነበር። ፍናና ብዙ ልጆች ነበሯት፤ ሐና ግን ምንም ልጅ አልነበራትም፤ ስለዚህ ፍናና ሁልጊዜ በሐና ላይ ታሾፍባት ነበር። ሕልቃና በሴሎ በሚገኘው የማደሪያ ድንኳን ይሖዋን ለማምለክ በየዓመቱ ቤተሰቡን ይዞ ይሄድ ነበር። በአንድ ወቅት ወደ ሴሎ ሄደው ሳለ ሕልቃና የሚወዳት ሚስቱ ሐና በጣም እንዳዘነች አስተዋለ። ስለዚህ ‘ሐና፣ እባክሽ አታልቅሺ። እኔ አለሁልሽ። እኔ እኮ በጣም ነው የምወድሽ’ አላት።

በኋላም ሐና ብቻዋን ሆና ለመጸለይ ሄደች። ይሖዋን እንዲረዳት እያለቀሰች ለመነችው። እንዲህ በማለት ቃል ገባች፦ ‘ይሖዋ ሆይ፣ ወንድ ልጅ ብትሰጠኝ ለአንተ እሰጠዋለሁ፤ እሱም ዕድሜውን ሙሉ ያገለግልሃል።’

ሊቀ ካህናቱ ኤሊ ሐና እያለቀሰች ስትጸልይ ሲያያት

ሊቀ ካህናቱ ኤሊ፣ ሐና እያለቀሰች ስትጸልይ ሲያይ የሰከረች መሰለው። ሐናም እንዲህ አለችው፦ ‘ሰክሬ አይደለም ጌታዬ። ከባድ ችግር ስላለብኝ ይሖዋ እንዲረዳኝ እየለመንኩት ነው።’ ኤሊም እንደተሳሳተ ሲገባው ‘አምላክ የምትፈልጊውን ነገር ይስጥሽ’ አላት። ሐናም ተጽናንታ ሄደች። ከዚያም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ስሙንም ሳሙኤል አለችው። ሐና ልጅ በማግኘቷ ምን ያህል ተደስታ ሊሆን እንደሚችል አስበው።

ሐና ለይሖዋ የገባችውን ቃል አልረሳችም። ልክ ሳሙኤል ጡት መጥባት እንዳቆመ ወደ ማደሪያ ድንኳኑ አመጣችው። ከዚያም ኤሊን እንዲህ አለችው፦ ‘ስጸልይ የነበረው ይህን ልጅ ለማግኘት ነበር። በሕይወቱ ሙሉ ይሖዋን እንዲያገለግል ለእሱ እሰጠዋለሁ።’ ሕልቃናና ሐና በየዓመቱ ሳሙኤልን ለመጠየቅ ወደ ማደሪያ ድንኳኑ ሲሄዱ አዲስ ልብስ ያመጡለት ነበር። ይሖዋ ከዚያ በኋላ ለሐና ሌሎች ሦስት ወንዶችና ሁለት ሴቶች ልጆች ሰጣት።

“ደጋግማችሁ ለምኑ፣ ይሰጣችኋል፤ ሳታቋርጡ ፈልጉ፣ ታገኛላችሁ።”—ማቴዎስ 7:7

ጥያቄ፦ ሐና ያዘነችው ለምንድን ነው? ይሖዋ ሐናን የባረካት እንዴት ነው?

1 ሳሙኤል 1:1–2:11, 18-21

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ