የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 40 ገጽ 98-ገጽ 99 አን. 2
  • ዳዊት እና ጎልያድ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ዳዊት እና ጎልያድ
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • “ውጊያው የይሖዋ ነው”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
  • ዳዊትና ጎልያድ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ዳዊት አልፈራም
    ልጆቻችሁን አስተምሩ
  • ዳዊት ያልፈራው ለምን ነበር?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2008
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 40 ገጽ 98-ገጽ 99 አን. 2
ዳዊት ጎልያድ ላይ ድንጋይ ሲወነጭፍ

ትምህርት 40

ዳዊት እና ጎልያድ

ይሖዋ ሳሙኤልን እንዲህ አለው፦ ‘ወደ እሴይ ቤት ሂድ። ከእሴይ ልጆች መካከል አንዱ ቀጣዩ የእስራኤል ንጉሥ ይሆናል።’ ስለዚህ ሳሙኤል ወደ እሴይ ቤት ሄደ። ከዚያም የመጀመሪያ ልጁን ሲያይ ‘ይሖዋ የመረጠው ይህን ወጣት መሆን አለበት’ ብሎ አሰበ። ይሖዋ ግን ሳሙኤልን ‘የመረጥኩት እሱን አይደለም። እኔ የማየው የሰውን መልክ ብቻ ሳይሆን እውነተኛ ባሕርይውን ጭምር ነው’ አለው።

ሳሙኤል ዳዊትን ሲቀባው

እሴይ ሌሎቹን ስድስት ልጆቹን ጠርቶ ሳሙኤል ፊት አቀረባቸው። ሳሙኤል ግን ‘ይሖዋ እነዚህንም አልመረጣቸውም። ሌላ ልጅ የለህም?’ አለው። እሴይም ‘የመጨረሻው ልጄ ዳዊት አለ። ውጭ በጎቹን እየጠበቀ ነው’ አለ። ዳዊት ወደ ቤት ሲገባ ይሖዋ ሳሙኤልን ‘የመረጥኩት እሱን ነው!’ አለው። ሳሙኤልም በዳዊት ራስ ላይ ዘይት በማፍሰስ ቀጣዩ የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆን ቀባው።

ከተወሰነ ጊዜ በኋላ እስራኤላውያን ከፍልስጤማውያን ጋር ለመዋጋት ተሰለፉ፤ ፍልስጤማውያን ጎልያድ የሚባል ግዙፍ ተዋጊ ነበራቸው። ጎልያድ በየቀኑ በእስራኤላውያን ላይ ያሾፍ ነበር። ‘ከእኔ ጋር የሚዋጋ ሰው ካለ ይምጣ። እሱ ካሸነፈኝ እኛ የእናንተ ባሪያዎች እንሆናለን። እኔ ካሸነፍኩት ደግሞ እናንተ የእኛ ባሪያዎች ትሆናላችሁ’ እያለ ይጮኽ ነበር።

ጎልያድ

የዳዊት ወንድሞች ወታደሮች ስለነበሩ ዳዊት ለእነሱ ምግብ ለማድረስ ወደ እስራኤል ጦር ሰፈር መጣ። ከዚያም ጎልያድ የሚናገረውን ሲሰማ ‘እኔ እዋጋዋለሁ!’ አለ። ንጉሥ ሳኦል ግን ‘አንተ እኮ ገና ልጅ ነህ’ አለው። ዳዊትም ‘ይሖዋ ይረዳኛል’ በማለት መለሰ።

ሳኦል የጦር ልብሱን ለዳዊት ሊሰጠው ፈልጎ ነበር፤ ዳዊት ግን ‘ይህን ለብሼ መዋጋት አልችልም’ አለ። ከዚያም ዳዊት ወንጭፉን ይዞ ወደ ወንዝ ሄደ። አምስት ድቡልቡል ድንጋዮች መረጠና ኮሮጆው ውስጥ ጨመራቸው። ከዚያም ወደ ጎልያድ እየሮጠ ሄደ። ጎልያድም ‘እስቲ ወደዚህ ና። ሥጋህን ለሰማይ አሞሮችና ለምድር አራዊት እሰጣለሁ’ በማለት ጮኸበት። ዳዊት ግን አልፈራም። ከዚህ ይልቅ እንዲህ አለው፦ ‘አንተ ሰይፍና ጦር ይዘህ ትመጣብኛለህ፤ እኔ ግን በይሖዋ ስም እመጣብሃለሁ። የምትዋጋው ከእኛ ጋር ሳይሆን ከአምላክ ጋር ነው። እዚህ ያሉት ሰዎች ሁሉ ይሖዋ ከሰይፍ ወይም ከጦር የበለጠ ኃይል እንዳለው ያያሉ። ሁላችሁንም በእጃችን አሳልፎ ይሰጣችኋል።’

ዳዊትም አንድ ድንጋይ ወንጭፉ ላይ አድርጎ ባለ በሌለ ኃይሉ አሽከረከረው። ይሖዋ ዳዊትን ስለረዳው ድንጋዩ ሄዶ የጎልያድ ግንባር ውስጥ ተቀረቀረ። ከዚያም ግዙፉ ጎልያድ መሬት ላይ ተደፋ፤ በዚህ ሁኔታ ዳዊት ጎልያድን ገደለው። ፍልስጤማውያንም ሸሹ። አንተስ እንደ ዳዊት በይሖዋ ትተማመናለህ?

“ይህ በሰዎች ዘንድ አይቻልም፤ በአምላክ ዘንድ ግን እንዲህ አይደለም፤ በአምላክ ዘንድ ሁሉ ነገር ይቻላል።”—ማርቆስ 10:27

ጥያቄ፦ ይሖዋ ቀጣዩ የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆን የመረጠው ማንን ነው? ዳዊት ጎልያድን ያሸነፈው እንዴት ነው?

1 ሳሙኤል 16:1-13፤ 17:1-54

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ