የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 44 ገጽ 108-ገጽ 109 አን. 3
  • የይሖዋ ቤተ መቅደስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የይሖዋ ቤተ መቅደስ
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሰሎሞን ቤተ መቅደሱን ሠራ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ሰለሞን ጠቢብ ንጉሥ ነበር
    መጽሐፍ ቅዱስ—የያዘው መልእክት ምንድን ነው?
  • ጥሩ አርዓያም የማስጠንቀቂያ ምሳሌም ሊሆነን የሚችል ሰው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
  • ከፍተኛ ወሮታ ያስገኘ ጉብኝት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1999
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 44 ገጽ 108-ገጽ 109 አን. 3
እሳት ከሰማይ ወርዶ በመሠዊያው ላይ ያለውን መሥዋዕት ሲበላ

ትምህርት 44

የይሖዋ ቤተ መቅደስ

ንጉሥ ሰለሞን ሲጸልይ

ሰለሞን የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ በኋላ ይሖዋ ‘ምን እንድሰጥህ ትፈልጋለህ?’ በማለት ጠየቀው። ሰለሞንም እንዲህ አለ፦ ‘እኔ ገና ልጅ ነኝ፤ ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላውቅም። እባክህ ሕዝብህን መምራት እንድችል ጥበብ ስጠኝ።’ ከዚያም ይሖዋ እንዲህ አለው፦ ‘ጥበብ እንድሰጥህ ስለጠየቅክ በምድር ላይ ካሉ ሰዎች ሁሉ የበለጠ ጥበበኛ አደርግሃለሁ። ብዙ ሀብትም እሰጥሃለሁ። እኔን ከታዘዝክ ረጅም ዕድሜ ትኖራለህ።’

ሰለሞን ቤተ መቅደሱን መገንባት ጀመረ። ምርጥ የሆነውን ወርቅ፣ ብር፣ እንጨትና ድንጋይ ተጠቅሞ ቤተ መቅደሱን ገነባ። በሺዎች የሚቆጠሩ ጥሩ ችሎታ ያላቸው ወንዶችና ሴቶች ቤተ መቅደሱን በመገንባቱ ሥራ ተካፍለዋል። ከሰባት ዓመት በኋላ ቤተ መቅደሱ ተሠርቶ አለቀ፤ ከዚያም ቤተ መቅደሱን ለይሖዋ ለመወሰን ዝግጅት ተደረገ። በዚያም መሠዊያ ይገኝ የነበረ ሲሆን ቤተ መቅደሱ ለይሖዋ በተወሰነበት ጊዜ መሠዊያው ላይ መሥዋዕት ቀርቦ ነበር። ሰለሞን በመሠዊያው ፊት ተንበርክኮ እንዲህ በማለት ጸለየ፦ ‘ይሖዋ ሆይ፣ የዚህ ቤተ መቅደስ መጠንም ሆነ ውበት ለአንተ በጣም ያንስሃል፤ ግን እባክህ አምልኳችንን ተቀበል፤ ጸሎታችንንም ስማ።’ ታዲያ ይሖዋ ሰለሞን የገነባውን ቤተ መቅደስም ሆነ ያቀረበውን ጸሎት ተቀብሎታል? ሰለሞን ጸሎቱን እንደጨረሰ እሳት ከሰማይ ወርዶ በመሠዊያው ላይ የቀረበውን መሥዋዕት አቃጠለ። ይሖዋ በዚህ መንገድ ቤተ መቅደሱን እንደተቀበለው አሳየ። እስራኤላውያንም ይህን ሲያዩ በጣም ተደሰቱ።

እሳት ከሰማይ ወርዶ በመሠዊያው ላይ ያለውን መሥዋዕት ሲበላ

በመላው እስራኤልም ሆነ ራቅ ብለው በሚገኙ ቦታዎች የነበሩ ሰዎች በንጉሥ ሰለሞን ጥበብ ይደነቁ ነበር። ሰዎች ችግር ሲገጥማቸው መፍትሔ ለማግኘት ወደ ሰለሞን ይመጡ ነበር። የሳባ ንግሥትም ከባድ ጥያቄዎች በመጠየቅ ልትፈትነው መጥታ ነበር። ለጥያቄዎቿ የሰጠውን መልስ ስትሰማ ግን እንዲህ አለች፦ ‘ሰዎች ስለ አንተ የነገሩኝን ነገር አላመንኩም ነበር፤ አሁን ግን እነሱ ከተናገሩትም በላይ ጥበበኛ እንደሆንክ አይቻለሁ። አምላክህ ይሖዋ ባርኮሃል።’ ሰለሞን ይገዛ በነበረበት ዘመን እስራኤላውያን አስደሳች ሕይወት ይኖሩ ነበር። ሆኖም ከጊዜ በኋላ ሁኔታዎች ተለወጡ።

“ከሰለሞን የሚበልጥ እዚህ አለ።”—ማቴዎስ 12:42

ጥያቄ፦ ይሖዋ ለሰለሞን ለየት ያለ ጥበብ የሰጠው ለምንድን ነው? ይሖዋ ቤተ መቅደሱን እንደተቀበለው ያሳየው እንዴት ነው?

1 ነገሥት 2:12፤ 3:4-28፤ 4:29–5:18፤ 6:37, 38፤ 7:15–8:66፤ 10:1-13፤ 2 ዜና መዋዕል 7:1፤ 9:22

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ