የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 45 ገጽ 110-ገጽ 111 አን. 1
  • የእስራኤል መንግሥት ተከፈለ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የእስራኤል መንግሥት ተከፈለ
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የእስራኤል መንግሥት ተከፋፈለ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ይሖዋ ታማኞቹን አይጥልም
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2008
  • የአምላክን ሞገስ ማግኘት ይችል ነበር
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
  • የአንደኛ ነገሥት መጽሐፍ ጎላ ያሉ ነጥቦች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 45 ገጽ 110-ገጽ 111 አን. 1
አኪያህ በኢዮርብዓም ፊት ልብሱን 12 ቦታ ሲቀደው

ትምህርት 45

የእስራኤል መንግሥት ተከፈለ

ሰለሞን ይሖዋን ያመልክ በነበረበት ጊዜ ሁሉ በእስራኤል ውስጥ ሰላም ነበር። ሆኖም ሰለሞን ከተለያዩ አገሮች የመጡ ብዙ ሚስቶችን አገባ፤ እነዚህ ሴቶች ደግሞ ጣዖት ያመልኩ ነበር። ከጊዜ በኋላ ሰለሞንም ጣዖት ማምለክ ጀመረ። ይሖዋ በዚህ በጣም ተናደደ። ስለዚህ ሰለሞንን እንዲህ አለው፦ ‘የእስራኤል መንግሥት ለሁለት ይከፈላል። ትልቁን ክፍል ከአንተ ቤተሰብ ላይ ወስጄ ከአገልጋዮችህ ለአንዱ እሰጠዋለሁ፤ የአንተ ቤተሰብ የሚገዛው ትንሹን ብቻ ይሆናል።’

ይሖዋ ይህን ውሳኔውን በሌላ መንገድም ገለጸ። ከሰለሞን አገልጋዮች አንዱ የሆነው ኢዮርብዓም በመንገድ ላይ ሲሄድ ነቢዩ አኪያህን አገኘው። አኪያህም የራሱን ልብስ 12 ቦታ ቀደደና ኢዮርብዓምን እንዲህ አለው፦ ‘ይሖዋ የእስራኤልን መንግሥት ከሰለሞን ቤተሰብ ወስዶ ለሁለት ይከፍለዋል። አንተ በአሥር ነገዶች ላይ ንጉሥ ስለምትሆን አሥሩን ቁራጭ ውሰድ።’ ንጉሥ ሰለሞን ይህን ሲሰማ ኢዮርብዓምን ለመግደል ፈለገ! ስለዚህ ኢዮርብዓም ወደ ግብፅ ሸሸ። ከጊዜ በኋላ ሰለሞን ሞተና ልጁ ሮብዓም ነገሠ። በዚህ ጊዜ ኢዮርብዓም ወደ እስራኤል ቢመለስ ምንም ችግር እንደማያጋጥመው ተሰማው።

እስራኤላውያን ኢዮርብዓም ላቆመው የወርቅ ጥጃ መሥዋዕት ሲያቀርቡ

የእስራኤል ሽማግሌዎች ሮብዓምን ‘ለሕዝቡ መልካም ነገር የምታደርግ ከሆነ ለአንተ ታማኝ ይሆናሉ’ አሉት። ወጣት ጓደኞቹ ግን ‘ሕዝቡን በጭካኔ መግዛት አለብህ! እንዲያውም የበለጠ እንዲሠሩ አድርጋቸው!’ አሉት። ሮብዓም የወጣቶቹን ምክር ተቀበለ። ሕዝቡን በጭካኔ ይገዛ ጀመር፤ ስለዚህ አሥሩ የእስራኤል ነገዶች በሮብዓም ላይ ዓመፁ። ከዚያም ኢዮርብዓምን በአሥሩ ነገዶች ላይ ንጉሥ አደረጉት፤ ይህ የአሥሩ ነገድ መንግሥት የእስራኤል መንግሥት ተብሎ ይጠራ ጀመር። የቀሩት ሁለት ነገዶች መንግሥት ደግሞ የይሁዳ መንግሥት ተብሎ ይጠራ ጀመር፤ ሁለቱ ነገዶች ለሮብዓም ታማኝ ሆኑ። በዚህ መንገድ አሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ተከፈሉ።

ኢዮርብዓም ሕዝቡ ለአምልኮ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲሄድ አልፈለገም፤ ምክንያቱም ኢየሩሳሌም የምትገኘው በሮብዓም ግዛት ውስጥ ነበር። ኢዮርብዓም ‘ሕዝቡ ወደዚያ ከሄደ በእኔ ላይ ዓምፆ ሮብዓምን ሊደግፍ ይችላል’ ብሎ አሰበ። ስለዚህ ሁለት የወርቅ ጥጃዎች ሠርቶ እስራኤላውያንን እንዲህ አላቸው፦ ‘ኢየሩሳሌም በጣም ይርቃችኋል። እዚሁ ማምለክ ትችላላችሁ።’ በመሆኑም ሕዝቡ እንደገና ይሖዋን ትቶ የወርቅ ጥጃዎቹን ማምለክ ጀመረ።

“ከማያምኑ ጋር አቻ ባልሆነ መንገድ አትጠመዱ። ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ኅብረት አለው? . . . ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ድርሻ አለው?”—2 ቆሮንቶስ 6:14, 15

ጥያቄ፦ የእስራኤል መንግሥት የተከፈለው ለምን ነበር? ንጉሥ ሮብዓምና ንጉሥ ኢዮርብዓም ምን መጥፎ ነገሮችን ሠርተዋል?

1 ነገሥት 11:1-13, 26-43፤ 12:1-33

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ