የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 54 ገጽ 130-ገጽ 131 አን. 1
  • ይሖዋ ዮናስን በትዕግሥት አስተማረው

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ይሖዋ ዮናስን በትዕግሥት አስተማረው
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ምሕረት ስለ ማሳየት ትምህርት አግኝቷል
    በእምነታቸው ምሰሏቸው
  • ምሕረት ስለ ማሳየት ትምህርት አግኝቷል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
  • ዮናስ ስለ ይሖዋ ምሕረት ትምህርት አገኘ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1996
  • ዮናስና ትልቁ ዓሣ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 54 ገጽ 130-ገጽ 131 አን. 1
አንድ ግዙፍ ዓሣ እየዋኘ ሳለ ዮናስ ባሕሩ ውስጥ ሲሰምጥ

ትምህርት 54

ይሖዋ ዮናስን በትዕግሥት አስተማረው

የአሦር ከተማ በሆነችው በነነዌ የሚኖሩት ሰዎች በጣም ክፉዎች ነበሩ። ይሖዋ ነቢዩ ዮናስን ‘ወደ ነነዌ ሰዎች ሄደህ ክፉ ሥራችሁን ተዉ ብለህ ንገራቸው’ ብሎ አዘዘው። ዮናስ ግን ወደ ነነዌ መሄድ ሲገባው አቅጣጫውን ቀይሮ ወደ ተርሴስ የሚሄድ መርከብ ላይ ተሳፈረ።

መርከቡ በባሕሩ ላይ እየሄደ ሳለ ከባድ ማዕበል ስለተነሳ መርከበኞቹ በጣም ፈሩ። በመሆኑም ‘ይህ የደረሰብን ለምንድን ነው?’ ብለው ወደ አምላኮቻቸው ጸለዩ። በመጨረሻም ዮናስ እንዲህ አላቸው፦ ‘ይህ የደረሰባችሁ በእኔ ምክንያት ነው። እኔ ይሖዋ ያዘዘኝን ነገር ትቼ ወደ ሌላ ቦታ እየሄድኩ ነው። እኔን ወደ ባሕሩ ከጣላችሁኝ ማዕበሉ ይቆማል።’ መርከበኞቹ ዮናስን ሊጥሉት አልፈለጉም፤ ዮናስ ግን እንዲጥሉት በተደጋጋሚ ነገራቸው። ከዚያም ዮናስን ወደ ባሕሩ ሲወረውሩት ማዕበሉ ቆመ።

ዮናስ የሚሞት መስሎት ነበር። ባሕሩ ውስጥ እየሰመጠ ሲሄድ ወደ ይሖዋ ጸለየ። ይሖዋም አንድ ትልቅ ዓሣ ላከለት። ዓሣው ዮናስን ዋጠው፤ ዮናስ ግን አልሞተም። ዮናስ በዓሣው ውስጥ ሆኖ ‘ከዚህ በኋላ ሁልጊዜ አንተን እታዘዛለሁ’ በማለት ወደ ይሖዋ ጸለየ። ይሖዋም ዮናስን ለሦስት ቀናት ዓሣው ውስጥ አቆየው፤ ከዚያም ዓሣው ዮናስን ደረቅ ምድር ላይ እንዲተፋው አደረገ።

ዮናስ ከባሕሩ ከወጣ በኋላ ይሖዋ ወደ ነነዌ እንዲሄድ በድጋሚ አዘዘው። በዚህ ጊዜ ግን ዮናስ የተባለውን አደረገ። ወደ ነነዌ ሄዶ እነዚያን ክፉ ሰዎች ‘ነነዌ በ40 ቀን ውስጥ ትጠፋለች’ አላቸው። ከዚያም አንድ ያልተጠበቀ ነገር ተከሰተ፤ የነነዌ ሰዎች የዮናስን መልእክት ሰምተው ክፉ ነገር መሥራት አቆሙ። የነነዌ ንጉሥ ሕዝቡን እንዲህ አላቸው፦ ‘ወደ አምላክ ጸልዩ፤ ንስሐም ግቡ። ምናልባት ምሕረት ያደርግልን ይሆናል።’ ይሖዋ የነነዌ ሰዎች ንስሐ መግባታቸውን ሲያይ ነነዌን ሳያጠፋት ቀረ።

ዮናስ ወደ ነነዌ ሲገባ

ዮናስ ከተማዋ ስላልጠፋች በጣም ተበሳጨ። እስቲ አስበው፦ ይሖዋ ለዮናስ ትዕግሥትና ምሕረት አሳይቶታል፤ ዮናስ ግን የነነዌ ሰዎች ምሕረት እንዲደረግላቸው አልፈለገም። በመሆኑም ከከተማዋ ወጣና በአንዲት የቅል ተክል ጥላ ሥር አኩርፎ ተቀመጠ። ከዚያም የቅል ተክሏ ደረቀች፤ በዚህ ጊዜ ዮናስ በጣም ተናደደ። ስለዚህ ይሖዋ እንዲህ አለው፦ ‘አንተ ይህች ተክል ስለደረቀች አዘንክ። እኔስ በነነዌ ለሚኖሩ ሰዎች ማዘን የለብኝም? ንስሐ ስለገቡ አላጠፋኋቸውም።’ ይሖዋ ዮናስን ሊያስተምረው የፈለገው ነገር ምን ነበር? በነነዌ የሚኖሩ ሰዎች ሕይወት ከየትኛውም ተክል የበለጠ ዋጋ እንዳለው ሊያስተምረው ፈልጎ ነበር።

“ይሖዋ . . . እናንተን የታገሠው፣ ሁሉ ለንስሐ እንዲበቃ እንጂ ማንም እንዲጠፋ ስለማይፈልግ ነው።”—2 ጴጥሮስ 3:9

ጥያቄ፦ ይሖዋ ለዮናስ ምን ትምህርት ሰጠው? ከዮናስ ታሪክ ምን እንማራለን?

ዮናስ 1:1–4:11

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ