የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 62 ገጽ 148
  • በትልቅ ዛፍ የተመሰለ መንግሥት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • በትልቅ ዛፍ የተመሰለ መንግሥት
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የትልቁን ዛፍ ምሥጢር መግለጥ
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
  • ለዘላለም ጸንቶ የሚኖር መንግሥት
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • የአንድ ግዙፍ ምስል አነሳስና አወዳደቅ
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
  • በመጽሐፍ ቅዱስ የዘመን ስሌት መሠረት 1914 ምን የሆነበት ዓመት ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 62 ገጽ 148
ንጉሥ ናቡከደነጾር በሕልሙ ያየው ዛፍ ሲቆረጥ

ትምህርት 62

በትልቅ ዛፍ የተመሰለ መንግሥት

አንድ ቀን ናቡከደነጾር ተኝቶ ሳለ የሚያስፈራ ሕልም አየ። በመሆኑም የባቢሎንን ጥበበኛ ሰዎች አስጠርቶ የሕልሙን ትርጉም ጠየቃቸው። ሆኖም አንዳቸውም ትርጉሙን ሊነግሩት አልቻሉም። በመጨረሻም ዳንኤልን አስጠራውና የሕልሙን ትርጉም ጠየቀው።

ናቡከደነጾር ዳንኤልን እንዲህ አለው፦ ‘በሕልሜ አንድ ዛፍ አየሁ። ዛፉ በጣም አድጎ ሰማይ ደረሰ። ከየትም ቦታ ሆኖ ይህን ዛፍ ማየት ይቻል ነበር። የሚያማምሩ ቅጠሎችና ብዙ ፍሬዎች ነበሩት። እንስሳት በጥላው ሥር ያርፉ፣ ወፎችም በቅርንጫፎቹ ላይ ጎጇቸውን ይሠሩ ነበር። ከዚያም አንድ መልአክ ከሰማይ ወረደ። እንዲህም አለ፦ “ዛፉን ቁረጡ፤ ቅርንጫፎቹንም ጨፍጭፉ። ጉቶው ግን በብረትና በመዳብ ታስሮ ከነሥሩ መሬት ውስጥ ይቆይ። ልቡ ከሰው ልብ ይለወጥ፤ የአውሬም ልብ ይሰጠው፤ እንደዚያም ሆኖ ለሰባት ዘመናት ይቆይ። ሁሉም ሰዎች አምላክ በሁሉም ላይ ገዢ እንደሆነና መንግሥቱን ለፈለገው ሰው እንደሚሰጥ ይገነዘባሉ።”’

ይሖዋ ለዳንኤል የዚህን ሕልም ትርጉም ገለጠለት። ዳንኤል የሕልሙን ትርጉም ሲረዳ ደነገጠ። ከዚያም ንጉሡን እንዲህ አለው፦ ‘ንጉሥ ሆይ፣ ሕልሙ ስለ ጠላቶችህ ቢሆን ደስ ይለኝ ነበር፤ ሆኖም ሕልሙ አንተን የሚመለከት ነው። የተቆረጠው ትልቅ ዛፍ አንተ ነህ። መንግሥትህ ከአንተ ይወሰዳል፤ እንዲሁም እንደ ዱር እንስሳ በሜዳ ላይ ሣር ትበላለህ። ሆኖም መልአኩ ጉቶው ከነሥሩ መሬት ውስጥ እንደሚቆይ ስለተናገረ በድጋሚ ንጉሥ ትሆናለህ።’

ከአንድ ዓመት በኋላ አንድ ቀን ንጉሡ በቤተ መንግሥቱ ሰገነት ላይ እየተመላለሰ ባቢሎንን በአድናቆት ይመለከት ነበር። ከዚያም እንዲህ አለ፦ ‘የገነባኋትን አስደናቂ ከተማ ተመልከቱ። እንደ እኔ ያለ ታላቅ ንጉሥ የለም!’ ልክ እየተናገረ ሳለ ከሰማይ የመጣ አንድ ድምፅ ‘ናቡከደነጾር! አሁን መንግሥትህ ከአንተ ተወስዷል’ አለው።

ወዲያውኑ ናቡከደነጾር አእምሮውን ስቶ እንደ ዱር እንስሳ ሆነ። ስለሆነም ከቤተ መንግሥቱ ወጥቶ ከዱር እንስሳት ጋር መኖር ጀመረ። የናቡከደነጾር ፀጉር እንደ ንስር ላባ ረዘመ፤ ጥፍሮቹም አድገው እንደ ወፍ ጥፍሮች ሆኑ።

ሰባት ዓመታት ካለፉ በኋላ ናቡከደነጾር እንደገና ጤናማ ሆነ፤ ይሖዋም የባቢሎን ንጉሥ አደረገው። ከዚያም ናቡከደነጾር እንዲህ አለ፦ ‘የሰማያት ንጉሥ የሆነውን ይሖዋን አወድሳለሁ። አሁን ይሖዋ በሁሉም ላይ ገዢ እንደሆነ ተገንዝቤያለሁ። ኩራተኞችን ያዋርዳል፤ ንጉሣዊ ሥልጣንንም ለፈለገው ሰው መስጠት ይችላል።’

“ኩራት ጥፋትን፣ የትዕቢት መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል።”—ምሳሌ 16:18

ጥያቄ፦ የናቡከደነጾር ሕልም ትርጉም ምንድን ነው? ናቡከደነጾር ምን ትምህርት አገኘ?

ዳንኤል 4:1-37

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ