የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • lfb ትምህርት 64 ገጽ 152-ገጽ 153 አን. 4
  • ዳንኤል አንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ተጣለ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ዳንኤል አንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ተጣለ
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ዳንኤል በአንበሶች ጉድጓድ ውስጥ
    የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ
  • ከአንበሶች መንጋጋ ዳነ!
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
  • ዳንኤል አምላክን ያለማቋረጥ አገልግሏል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1996
  • ዳርዮስ የፍትሕ ዝንባሌ የነበረው ንጉሥ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1998
ለተጨማሪ መረጃ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
lfb ትምህርት 64 ገጽ 152-ገጽ 153 አን. 4
ሰዎች ዳንኤልን መስኮት አጠገብ ሲጸልይ አገኙት

ትምህርት 64

ዳንኤል አንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ተጣለ

በባቢሎን ላይ የነገሠው ሌላው ንጉሥ ደግሞ ሜዶናዊው ዳርዮስ ነበር። ዳርዮስ፣ ዳንኤል ከሌሎቹ ባለሥልጣናት ሁሉ የተለየ እንደሆነ አስተዋለ። ስለዚህ ዳንኤልን በባለሥልጣናቱ ላይ ሾመው። እነዚህ ሰዎች በዳንኤል ስለቀኑ ሊገድሉት ፈለጉ። ዳንኤል በየቀኑ ሦስት ጊዜ ወደ ይሖዋ እንደሚጸልይ ያውቁ ነበር፤ ስለዚህ ዳርዮስን እንዲህ አሉት፦ ‘ንጉሥ ሆይ፣ ሁሉም ሰው ወደ አንተ ብቻ እንዲጸልይ የሚያዝዝ ሕግ ይውጣ። ይህን ሕግ የማያከብር ማንኛውም ሰው ወደ አንበሶች ጉድጓድ ይጣል።’ ዳርዮስ በሐሳባቸው ተስማማ፤ ስለዚህ በሕጉ ላይ ፈረመ።

ዳንኤል ስለ አዲሱ ሕግ እንደሰማ ወደ ቤቱ ሄደ። የቤቱም መስኮት ተከፍቶ ነበር፤ ዳንኤልም መስኮቱ አጠገብ ተንበርክኮ ወደ ይሖዋ ጸለየ። በዳንኤል የቀኑት ሰዎች በሩን በርግደው ሲገቡ ዳንኤልን ሲጸልይ አገኙት። ስለዚህ ወደ ዳርዮስ ሄደው እንዲህ አሉት፦ ‘ዳንኤል አንተን አይታዘዝም። በቀን ሦስት ጊዜ ወደ አምላኩ ይጸልያል።’ ዳርዮስ ዳንኤልን ይወደው ስለነበር እንዲሞት አልፈለገም። ቀኑን ሙሉ ዳንኤልን ማዳን የሚችልበትን መንገድ ሲያስብ ዋለ። ሆኖም ንጉሡ የፈረመበትን ሕግ ራሱም እንኳ ሊቀይረው አይችልም ነበር። ስለዚህ ዳንኤልን አስፈሪ አንበሶች ወዳሉበት ጉድጓድ እንዲጥሉት ትእዛዝ አስተላለፈ።

በዚያ ሌሊት ዳርዮስ የዳንኤል ነገር በጣም ስላስጨነቀው እንቅልፍ ሊወስደው አልቻለም። በጠዋት ወደ ጉድጓዱ ሄዶ ዳንኤልን ‘አምላክህ ከአንበሶቹ አድኖሃል?’ አለው።

በዚህ ጊዜ ዳርዮስ አንድ ድምፅ ሰማ። የሰማው የዳንኤልን ድምፅ ነበር! ዳንኤል ዳርዮስን እንዲህ አለው፦ ‘የይሖዋ መልአክ የአንበሶቹን አፍ ዘጋ። ስለዚህ አንበሶቹ ምንም አልጎዱኝም።’ ዳርዮስ ይህን ሲሰማ በጣም ተደሰተ! ዳንኤልን ከጉድጓዱ እንዲያወጡት አዘዘ። ዳንኤል ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰበትም ነበር። ከዚያም ንጉሡ ‘ዳንኤልን የከሰሱትን ሰዎች አምጥታችሁ ጉድጓዱ ውስጥ ጣሏቸው’ በማለት አዘዘ። እነዚያ ሰዎች ወደ ጉድጓዱ ሲጣሉ አንበሶቹ በሏቸው።

ዳርዮስ እንዲህ በማለት ለሕዝቡ ትእዛዝ አስተላለፈ፦ ‘ሁሉም ሰው የዳንኤልን አምላክ መፍራት አለበት። ምክንያቱም ዳንኤልን ከአንበሶቹ አድኖታል።’

አንተስ እንደ ዳንኤል በየቀኑ ወደ ይሖዋ ትጸልያለህ?

ዳንኤል በአንበሶች ጉድጓድ ውስጥ

“ይሖዋ፣ ለአምላክ ያደሩ ሰዎችን ከፈተና እንዴት እንደሚያድን . . . ያውቃል።”—2 ጴጥሮስ 2:9

ጥያቄ፦ ዳንኤል በቀን ሦስት ጊዜ ምን ያደርግ ነበር? ይሖዋ ዳንኤልን ያዳነው እንዴት ነው?

ዳንኤል 6:1-28

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ