የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w07 3/15 ገጽ 3
  • የክርስቶስ መምጣት ሊያስፈራን ይገባል?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የክርስቶስ መምጣት ሊያስፈራን ይገባል?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2007
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የክርስቶስ መምጣት ሲባል ምን ማለት ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • የክርስቶስ መመለስ
    ከቅዱሳን ጽሑፎች እየጠቀሱ ማመራመር
  • የክርስቶስ መምጣት ምን ያከናውናል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2007
  • ኢየሱስ የሚያበረታታ መልእክት ይዞ መጣ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2007
w07 3/15 ገጽ 3

የክርስቶስ መምጣት ሊያስፈራን ይገባል?

ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት ስታስብ በዓይነ ሕሊናህ የሚታይህ ምንድን ነው? እልቂት፣ ጥፋትና በሰው ልጆች ላይ የሚደርስ የቅጣት ፍርድ ነው? ወይስ ችግሮቻችንን ሁሉ ያስወግድልናል ብለህ ትጠብቃለህ? የክርስቶስ መምጣት ሊያስፈራን ይገባል? ወይስ በጉጉት የምንጠባበቀው ነገር መሆን አለበት?

መጽሐፍ ቅዱስ የክርስቶስን መምጣት አስመልክቶ “እነሆ፤ በደመና ይመጣል፤ . . . ዐይን ሁሉ ያየዋል፤ የምድርም ሕዝቦች ሁሉ ከእርሱ የተነሣ ዋይ ዋይ ይላሉ” ይላል። (ራእይ 1:7) ይህ መምጣት፣ ኢየሱስ ጻድቃንን ለመባረክና ክፉ ሰዎችን ለመቅጣት ወደፊት በሚገለጥበት ጊዜ የሚኖረውን ሁኔታ ያመለክታል።

ሐዋርያው ዮሐንስ የክርስቶስን መምጣት ከመፍራት ይልቅ በጉጉት ይጠባበቅ ነበር። ዮሐንስ ስለ ክርስቶስ መምጣትና በምድር ላይ ስለሚያስከትለው ውጤት በራእይ ከተመለከተ በኋላ “ጌታ ኢየሱስ ሆይ፤ ና” ሲል ከልብ በመነጨ ስሜት ጸልዮአል። (ራእይ 22:20) ታዲያ ‘የምድር ሕዝቦች ሁሉ ከእርሱ የተነሣ ዋይ ዋይ የሚሉት’ ለምንድን ነው? “ዐይን ሁሉ” የሚያየውስ በምን መንገድ ነው? የክርስቶስ መምጣት ምን ያከናውናል? በክርስቶስ መምጣት ላይ እምነት ማሳደራችን የሚጠቅመን እንዴት ነው? የሚቀጥለው ርዕስ ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ይሰጣል።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ