የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w09 11/1 ገጽ 4
  • የተሳሳተ ትምህርት 1፦ ነፍስ አትሞትም

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የተሳሳተ ትምህርት 1፦ ነፍስ አትሞትም
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ነፍስ ምንድን ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ነፍስ ምን ይላል?
    ስንሞት ምን እንሆናለን?
  • የማትሞት ነፍስ አለችህ?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2007
  • ነፍስ
    ከቅዱሳን ጽሑፎች እየጠቀሱ ማመራመር
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2009
w09 11/1 ገጽ 4

የተሳሳተ ትምህርት 1፦ ነፍስ አትሞትም

ይህ የተሳሳተ ትምህርት የመነጨው ከየት ነው?

“የጥንቶቹ የክርስትና ፈላስፎች፣ ነፍስ አትሞትም የሚለውን የግሪክ ጽንሰ ሐሳብ እንዲሁም አምላክ ነፍስን ከፈጠረ በኋላ አንድ ሰው በሚፀነስበት ጊዜ ወደ አካሉ ያስገባታል የሚለውን ትምህርት ተቀብለው ነበር።”—ዘ ኒው ኢንሳይክሎፒዲያ ብሪታኒካ (1988)፣ ጥራዝ 11፣ ገጽ 25

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

“ኀጢአት የምትሠራ ነፍስ እርሷ ትሞታለች።”—ሕዝቅኤል 18:4

መጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያውን ሰው አፈጣጠር በተመለከተ እንዲህ ይላል፦ “እግዚአብሔር አምላክ ከምድር ዐፈር ወስዶ ሰውን አበጀው፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስ እፍ አለበት፤ ሰውም ሕያው ነፍስ [በዕብራይስጥ፣ ነፈሽ] ሆነ።”—ዘፍጥረት 2:7

“ነፍስ” ተብሎ የተተረጎመው ነፈሽ የሚለው የዕብራይስጥ ቃል ‘የሚተነፍስ ፍጡር’ የሚል ፍቺ አለው። አምላክ የመጀመሪያውን ሰው አዳምን ሲፈጥረው ወደ አካሉ ያስገባው ሕይወቱን የሚያቆይ ኃይል እንጂ የማትሞት ነፍስ አይደለም፤ ይህ የሕይወት ኃይል በሰውነቱ ውስጥ እንዲቆይ አዳም መተንፈስ ነበረበት። ከዚህ አንጻር “ነፍስ” በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚያመለክተው የአንድን ሰው የተወሰነ ክፍል ሳይሆን በሕይወት ያለውን ግለሰብ እንዳለ ነው። አምላክ መጀመሪያ ለሰው የሰጠው ሕይወትን የሚያቆይ ኃይል ከሰው ከወጣ ነፍስ ማለትም ሰውየው ይሞታል።—ዘፍጥረት 3:19፤ ሕዝቅኤል 18:20

ነፍስ አትሞትም የሚለው መሠረተ ትምህርት የሚከተሉትን ጥያቄዎች አስነስቷል፦ ከሞት በኋላ ነፍስ ወዴት ትሄዳለች? የክፉዎች ነፍስ ምን ይሆናል? ስመ ክርስትና፣ ነፍስ አትሞትም የሚለውን የተሳሳተ ትምህርት መቀበሏ ሌላ የተሳሳተ ትምህርት ይኸውም የመቃጠያ እሳት አለ የሚለውን ጽንሰ ሐሳብ ወደ መቀበል መርቷታል።

እነዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች አወዳድር፦ መክብብ 3:19፤ ማቴዎስ 10:28፤ የሐዋርያት ሥራ 3:23

እውነታው፦

አንድ ሰው ሲሞት ከሕልውና ውጪ ይሆናል

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ