የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w15 6/1 ገጽ 6-7
  • ሳይንስ የደረሰባቸው ነገሮች ውስን ናቸው

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ሳይንስ የደረሰባቸው ነገሮች ውስን ናቸው
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ሳይንስ በሕይወትህ ላይ ምን ተጽዕኖ ያሳድራል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • የይሖዋ ምሥክሮች ስለ ሳይንስ ምን አመለካከት አላቸው?
    ስለ ይሖዋ ምሥክሮች ብዙ ጊዜ የሚነሱ ጥያቄዎች
  • ሳይንስና መጽሐፍ ቅዱስ ይስማማሉ?
    ንቁ!—2011
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
w15 6/1 ገጽ 6-7
አንዲት የሳይንስ ሊቅ በላብራቶሪ ውስጥ

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | መጽሐፍ ቅዱስ በሳይንስ ተተክቷል?

ሳይንስ የደረሰባቸው ነገሮች ውስን ናቸው

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አምላክ የለሾች ተብለው የሚጠሩትን ሰዎች አመለካከት የሚገልጹ በርካታ መጻሕፍት በሰፊው ተሰራጭተዋል። እነዚህ የኅትመት ውጤቶች የብዙዎችን ቀልብ የሳቡ ሲሆን ለብዙ ውይይትና ክርክር መነሻ ሆነዋል። ይህን በተመለከተ የነርቭ ሳይንስ ሊቅ የሆኑት ዴቪድ ኢግልማን “አንዳንድ አንባቢዎች . . . የሳይንስ ሊቃውንት ሁሉንም ነገር የሚያውቁ ይመስላቸዋል” በማለት ጽፈዋል። አክለውም “ጥሩ አመለካከት ያላቸው የሳይንስ ሊቃውንት ግን ምንጊዜም የሌሎችን ሐሳብ የሚቀበሉ ሲሆን ያስመዘገቡት ታሪክም ቢሆን አዳዲስና ያልተጠበቁ ግኝቶች የሞሉበት ነው” ብለዋል።

አንድ የሥነ ፈለክ ተመራማሪ በቴሌስኮፕ ሲመለከት

ባለፉት ዘመናት ሁሉ ተሰጥኦ ያላቸው የሳይንስ ሊቃውንት ተፈጥሮን በተመለከተ ግራ ለሚያጋቡ ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት ባደረጉት ጥረት አስገራሚ የሆኑ እመርታዎችን አስመዝግበዋል። ይሁን እንጂ አንዳንዶቹ፣ በዚህ ሂደት ውስጥ ከባድ ስህተቶችን ፈጽመዋል። አይዛክ ኒውተን ታላላቅ ከሚባሉት የሳይንስ ሊቃውንት አንዱ ነበር። ይህ የሳይንስ ሊቅ የስበት ኃይል ፕላኔቶችን፣ ከዋክብትንና የከዋክብት ረጨቶችን በጽንፈ ዓለም ውስጥ አንድ ላይ ተሳስረው እንዲቀመጡ የሚያደርጋቸው እንዴት እንደሆነ አሳይቷል። ለኮምፒውተር ንድፍ አወጣጥ፣ ለሕዋ ጉዞ እንዲሁም ለኑክሌር ፊዚክስ የሚያገለግል ካልኩለስ የሚባል የሒሳብ ዘርፍ ፈልስፏል። ይሁን እንጂ ኒውተን ኮከብ ቆጠራንና ምትሃታዊ ፎርሙላዎችን ተጠቅሞ የእርሳስ ማዕድንንና ሌሎች ብረቶችን ወደ ወርቅ ለመለወጥ ጥረት አድርጓል።

ከኒውተን በፊት ከ1,500 ከሚበልጡ ዓመታት ቀደም ብሎ ቶለሚ የሚባል የግሪክ የሥነ ፈለክ ተመራማሪ ሰማያትን በዓይኖቹ ብቻ በመቃኘት ምርምር ያደርግ ነበር። ምሽት ላይ በሰማይ የሚታዩት ፕላኔቶች የሚጓዙበትን መስመር ያጠና ሲሆን በካርታ ሥራም የተካነ ነበር። ይሁን እንጂ ምድር የሁሉም ነገር እምብርት ናት ብሎ ያምን ነበር። በከዋክብት ጥናት ምሁር የሆኑት ካርል ሳጋን ስለ ቶለሚ እንዲህ ብለው ጽፈዋል፦ “ምድርን ማዕከል ያደረገው [የቶለሚ] ጽንፈ ዓለም ከ1,500 ዓመታት በኋላ ተቀባይነት ማጣቱ አንድ ሰው ከፍተኛ እውቀት ያለው መሆኑ ምንም ስህተት እንዳይፈጽም ዋስትና እንደማይሆን የሚያስገነዝብ ነው።”

አንዲት የሳይንስ ሊቅ መጽሐፍ ቅዱስን ስታነብ

በዛሬው ጊዜም የሳይንስ ሊቃውንት ምርምር ሲያደርጉ ተመሳሳይ የሆነ ተፈታታኝ ሁኔታ ያጋጥማቸዋል። ጽንፈ ዓለምን በተመለከተ የተሟላ ማብራሪያ የማግኘታቸው ጉዳይ አጠያያቂ ነው። ሳይንስ እድገት እያደረገ እንደመጣና ጥቅም እንዳስገኘልን ባይካድም የደረሰባቸው ነገሮች ውስን መሆናቸውን ማስታወሳችን ተገቢ ነው። የፊዚክስ ሊቅ የሆኑት ፖል ዴቪስ የሚከተለውን ታዝበዋል፦ “ለሁሉም ነገር የተሟላና የማይለዋወጥ ማብራሪያ ለማግኘት መጣር ከንቱ ልፋት ነው።” ይህ አባባል አንድ የማይካድ ሐቅ ይኸውም ሰዎች ተፈጥሮን ሙሉ በሙሉ መረዳት እንደማይችሉ ያስገነዝባሉ። በመሆኑም ሳይንስ ወደ ሕልውና ስለመጣው ስለ እያንዳንዱ ነገር ማብራሪያ መስጠት ይችላል ተብሎ የሚነገረውን ነገር ከመቀበላችን በፊት በጥንቃቄ ማጤናችን ብልህነት ነው።

በግልጽ ማየት እንደሚቻለው መጽሐፍ ቅዱስ ከሳይንስ ልናገኝ የማንችለውን መመሪያ ይሰጠናል

መጽሐፍ ቅዱስ በተፈጥሮ ላይ ስለሚታዩት ድንቅ ነገሮች ሲናገር “እነሆ፣ እነዚህ የመንገዱ ዳር ዳር ናቸው፤ ስለ እሱ የሰማነው የሹክሹክታ ያህል ብቻ ነው!” ይላል። (ኢዮብ 26:14) ከሰው የማሰብም ሆነ የመረዳት ችሎታ በላይ የሆነ ብዙ የእውቀት ክምችት አለ። በእርግጥም ከ2,000 ዓመታት ገደማ በፊት የተጻፉት የሚከተሉት የሐዋርያው ጳውሎስ ቃላት ዛሬም እውነት ናቸው፦ “የአምላክ ብልጽግና፣ ጥበብና እውቀት እንዴት ጥልቅ ነው! ፍርዱም ፈጽሞ የማይመረመር ነው! መንገዱም የማይደረስበት ነው!”—ሮም 11:33

ከሳይንስ ልናገኝ የማንችለው መመሪያ

ሳይንስ ስለ ግዑዙ ዓለም እንድናውቅ የሚያደርግ ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ ከሰዎች ጋር ያለን ግንኙነት ሰላማዊ እንዲሆንና አርኪ የሆነ አስደሳች ሕይወት እንድንመራ የሚያስችሉ መመሪያዎችን ይሰጣል። ቀጥሎ የቀረቡትን ምሳሌዎች እንመልከት።

  • ቁም የሚል ምልክት

    ወንጀልን መከላከል

    ለሕይወት አክብሮት ይኑርህ

    “አትግደል።”—ዘፀአት 20:13

    “ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው።”—1 ዮሐንስ 3:15

    ሰላምን መፍጠርና ጠብቆ ማቆየት

    “ክፉ ከሆነ ነገር ራቅ፤ መልካም የሆነውንም አድርግ፤ ሰላምን ፈልግ፤ ተከተለውም።”—መዝሙር 34:14

    “የጽድቅ ፍሬ ሰላም ፈጣሪ ለሆኑ ሰዎች ሰላማዊ በሆኑ ሁኔታዎች ይዘራል።”—ያዕቆብ 3:18

    ከዓመፅ ራቅ

    “ይሖዋ ጻድቁንም ሆነ ክፉውን ይመረምራል፤ ክፋትን የሚወዱ ሰዎችን ይጠላል።”—መዝሙር 11:5

    “በዓመፀኛ ሰው አትቅና፤ የትኛውንም መንገዱን አትምረጥ፤ ይሖዋ ተንኮለኛን ሰው ይጸየፋል።”—ምሳሌ 3:31, 32

  • አንድ ቤተሰብ

    የቤተሰብ ደስታ

    ወላጆችህን ታዘዝ

    “ልጆች ሆይ፣ ከጌታ ፈቃድ ጋር በሚስማማ መንገድ ለወላጆቻችሁ ታዘዙ፤ ይህ የጽድቅ ተግባር ነውና። ‘አባትህንና እናትህን አክብር’ የሚለው የመጀመሪያው ትእዛዝ እንዲህ የሚል የተስፋ ቃል ይዟል፦ ‘ይህም መልካም እንዲሆንልህና ዕድሜህ በምድር ላይ እንዲረዝም ነው።’”—ኤፌሶን 6:1-3

    ልጆቻችሁን በሚገባ አስተምሩ

    “ልጆቻችሁን አታስመርሯቸው፤ ከዚህ ይልቅ በይሖዋ ተግሣጽና ምክር አሳድጓቸው።” —ኤፌሶን 6:4

    “ቅስማቸው እንዳይሰበር ልጆቻችሁን አታበሳጯቸው።”—ቆላስይስ 3:21

    የትዳር ጓደኛህን ውደድ እንዲሁም አክብር

    “ከእናንተ እያንዳንዱ ራሱን እንደሚወድ ሁሉ ሚስቱንም ይውደድ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ሚስት ባሏን በጥልቅ ታክብር።”—ኤፌሶን 5:33

  • ዛፍ

    ተፈጥሮን መንከባከብ

    በጥንቷ እስራኤል የተለያየ ዓይነት ብክለት የሚያደርሱ ሰዎችን በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስ “ምድሪቱ በገዛ ነዋሪዎቿ ተበክላለች። . . . በላይዋም የሚኖሩ ሰዎች በደለኞች ሆነው ተገኝተዋል” በማለት ተናግሮ ነበር። (ኢሳይያስ 24:5, 6) አምላክ ሆን ብለው ምድርን የሚያበላሹ ሰዎችን ተጠያቂ ያደርጋቸዋል። “ምድርን እያጠፉ ያሉትን [ያጠፋል]።” (ራእይ 11:18) እንዲህ የሚያደርጉ ሁሉ ከቅጣት አያመልጡም።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ