የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp16 ቁጥር 2 ገጽ 3-4
  • ታሪኩ እውነት ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ታሪኩ እውነት ነው?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ማስረጃዎቹ ምን ያሳያሉ?
  • ስለ ኢየሱስ ትንሣኤ ምን ማለት ይቻላል?
  • የኢየሱስ ትንሣኤ ለእኛ ምን ትርጉም አለው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2014
  • የኢየሱስ ትንሣኤ በእርግጥ ተፈጽሟል?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2013
  • ወንጌሎች—እውነተኛ ታሪክ ናቸው ወይስ ተረት?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2000
  • ትንሣኤ—አስተማማኝ ተስፋ!
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
wp16 ቁጥር 2 ገጽ 3-4
የኢየሱስን አስከሬን ከመከራው እንጨት ላይ ሲያወርዱት፤ ደቀ መዛሙርቱ ከርቀት ሆነው ሲመለከቱ

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | ኢየሱስ የተሠቃየውና የሞተው ለምንድን ነው?

ታሪኩ እውነት ነው?

በ33 ዓ.ም. በጸደይ ወቅት የናዝሬቱ ኢየሱስ ተገደለ። ኢየሱስ፣ ሕዝብን ለዓመፅ አነሳስቷል የሚል የሐሰት ክስ የተሰነዘረበት ሲሆን በጭካኔ ከተገረፈ በኋላ በእንጨት ላይ ተቸነከረ። የሞተውም እጅግ ተሠቃይቶ ነው። ይሁን እንጂ አምላክ ከሞት አስነሳው፤ ከ40 ቀን በኋላም ወደ ሰማይ አረገ።

ይህ አስገራሚ ዘገባ ተመዝግቦ የሚገኘው፣ በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት (በተለምዶ አዲስ ኪዳን ይባላሉ) ውስጥ ባሉት አራት ወንጌሎች ላይ ነው። ሆኖም ይህ ዘገባ እውነት ነው? ይህ አግባብነት ያለውና በቁም ነገር ሊታሰብበት የሚገባ ጥያቄ ነው። ምክንያቱም ዘገባው እውነት ካልሆነ የክርስትና እምነት ዋጋ ቢስ ይሆናል፤ በገነት ውስጥ የዘላለም ሕይወት የማግኘት ተስፋም እንዲሁ ምኞት ብቻ ሆኖ ይቀራል። (1 ቆሮንቶስ 15:14) በሌላ በኩል ደግሞ ዘገባው እውነት ከሆነ አንተን ጨምሮ መላው የሰው ዘር ብሩህ ተስፋ አለው ማለት ነው። ታዲያ የወንጌል ዘገባዎች እውነት ናቸው ወይስ ልብ ወለድ?

ማስረጃዎቹ ምን ያሳያሉ?

በምናብ ከተፈጠሩ አፈ ታሪኮች በተለየ መልኩ የወንጌል ጸሐፊዎች፣ ትክክለኛ ዘገባ ለማስፈር ከፍተኛ ጥረት እንዳደረጉና ለእያንዳንዱ ዝርዝር ጉዳይ ትኩረት እንደሰጡ ከዘገባው ማየት ይቻላል። ለምሳሌ ያህል፣ በዘገባዎቹ ላይ የብዙ ቦታዎች ስም የተጠቀሰ ሲሆን ከእነዚህ አብዛኞቹን አሁንም ሄዶ መጎብኘት ይቻላል። በዘገባዎቹ ላይ የተጠቀሱት ሰዎች በገሃዱ ዓለም ላይ የነበሩ ናቸው፤ ይህንንም የዓለም ታሪክ ምሁራን አረጋግጠዋል።—ሉቃስ 3:1, 2, 23

በመጀመሪያውና በሁለተኛው መቶ ዘመን የኖሩ የዓለም ታሪክ ጸሐፊዎች ኢየሱስን በጽሑፎቻቸው ላይ ጠቅሰውታል።a የተገደለበትን መንገድ በተመለከተ በወንጌል ዘገባዎች ላይ የሰፈረው ሐሳብ፣ በዘመኑ ሮማውያን የሞት ቅጣት ከሚፈጽሙበት መንገድ ጋር ይስማማል። በተጨማሪም ዘገባዎቹ በማስረጃ የተደገፉና ሐቀኝነት የሚንጸባረቅባቸው ናቸው፤ እንዲያውም ከኢየሱስ ደቀ መዛሙርት የአንዳንዶቹ ድክመት እንኳ በወንጌሎች ላይ ተካቷል። (ማቴዎስ 26:56፤ ሉቃስ 22:24-26፤ ዮሐንስ 18:10, 11) እነዚህ ሁሉ ማስረጃዎች፣ የወንጌል ጸሐፊዎች ስለ ኢየሱስ ያሰፈሩት ዘገባ እውነተኛና ትክክለኛ እንደሆነ በሚገባ ያሳያሉ።

ስለ ኢየሱስ ትንሣኤ ምን ማለት ይቻላል?

ኢየሱስ በአንድ ወቅት የነበረ ሰው መሆኑና መሞቱ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ቢያገኝም ከሞት መነሳቱን ግን የሚጠራጠሩ ሰዎች አሉ። የኢየሱስ ሐዋርያትም እንኳ ጌታቸው ትንሣኤ እንዳገኘ መጀመሪያ ሲነገራቸው አላመኑም ነበር። (ሉቃስ 24:11) ይሁን እንጂ እነዚህም ሆኑ ሌሎች ደቀ መዛሙርቱ፣ ትንሣኤ ያገኘውን ኢየሱስን በተለያዩ ወቅቶች ካዩት በኋላ የነበራቸው ጥርጣሬ በሙሉ ተወገደ። እንዲያውም ኢየሱስ ትንሣኤ ካገኘ በኋላ ከ500 ለሚበልጡ የዓይን ምሥክሮች የተገለጠበት ጊዜ አለ።—1 ቆሮንቶስ 15:6

ደቀ መዛሙርቱ ሊታሰሩና ሊገደሉ እንደሚችሉ እያወቁ፣ ኢየሱስ ከሞት መነሳቱን ለሁሉም ሰው ሌላው ቀርቶ እሱን ላስገደሉት ሰዎች እንኳ በድፍረት አውጀዋል። (የሐዋርያት ሥራ 4:1-3, 10, 19, 20፤ 5:27-32) እነዚያ ሁሉ ደቀ መዛሙርት፣ ኢየሱስ ከሞት እንደተነሳ ፍጹም እርግጠኞች ባይሆኑ ኖሮ የዚህን ያህል በልበ ሙሉነት ይናገሩ ነበር? እንዲያውም ክርስትና በዚያ ዘመንም ሆነ ዛሬ ባለው ዓለም ላይ ይህን ያህል ተጽዕኖ እንዲያሳድር ያደረገው ኢየሱስ ትንሣኤ ማግኘቱ ነው።

ስለ ኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ የሚገልጹት የወንጌል ዘገባዎች፣ ተአማኒ ታሪካዊ መዛግብት መሆናቸውን ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉትን መሥፈርቶች በሙሉ አሟልተዋል። ዘገባዎቹን በትኩረት ማንበብህ ታሪኩ እውነት መሆኑን እንድታምን ያደርግሃል። ኢየሱስ የሞተውና የተነሳው ለምን እንደሆነ ስትገነዘብ ደግሞ እምነትህ ይበልጥ ይጠናከራል። የሚቀጥለው ርዕስ ይህን ጉዳይ ያብራራል።

a በ55 ዓ.ም. ገደማ የተወለደው ታሲተስ እንዲህ ሲል ጽፏል፦ “[ክርስቲያኖች] ለሚለው ስም መገኛ የሆነው ክርስቱስ [ክርስቶስ] በጢባርዮስ የንግሥና ዘመን ከአስተዳዳሪዎቻችን አንዱ በነበረው በጳንጥዮስ ጲላጦስ እጅ ከፍተኛ የሆነ ቅጣት ተቀብሏል።” በተጨማሪም ስዊቶኒየስ (አንደኛው መቶ ዘመን)፣ አይሁዳዊው የታሪክ ምሁር ጆሴፈስ (አንደኛው መቶ ዘመን) እንዲሁም የቢቲኒያ አገረ ገዢ የነበረው ትንሹ ፕሊኒ (ሁለተኛው መቶ ዘመን መጀመሪያ) ኢየሱስን ጠቅሰውታል።

ዓለማዊ ምንጮች ሰፋ ያለ ዘገባ ያልያዙት ለምንድን ነው?

ኢየሱስ በዓለም ላይ ካሳደረው ከፍተኛ ተጽዕኖ አንጻር በዘመኑ የነበሩ ምንጮች (ከመጽሐፍ ቅዱስ ሌላ) ሰፋ ያለ ዘገባ እንደሚይዙ መጠበቅ ይኖርብናል? አይኖርብንም። ምክንያቱም አንደኛ ነገር፣ ወንጌሎች ከተጻፉ 2,000 ዓመት ገደማ ሆኗቸዋል። በዚያ ዘመን ከተዘጋጁ ሌሎች ጽሑፎች መካከል እስከ ዘመናችን ተጠብቀው የቆዩት በጣም ጥቂት ናቸው። (1 ጴጥሮስ 1:24, 25) ከዚህም ሌላ ኢየሱስ ብዙ ተቃዋሚዎች ነበሩት፤ በመሆኑም ሰዎች በእሱ እንዲያምኑ የሚያደርግ ነገር ይጽፋሉ ብሎ ማሰብ የማይመስል ነገር ነው።

ከሐዋርያቱ አንዱ የሆነው ጴጥሮስ የኢየሱስን ትንሣኤ በተመለከተ እንዲህ ብሏል፦ “አምላክ እሱን በሦስተኛው ቀን አስነሳው፤ ከዚያም ለሰዎች እንዲገለጥ አደረገው፤ የተገለጠው ግን ለሁሉም ሰው ሳይሆን አምላክ አስቀድሞ ለመረጣቸው ምሥክሮች ይኸውም ከሞት ከተነሳ በኋላ አብረነው ለበላንና ለጠጣን ለእኛ ነው።” (የሐዋርያት ሥራ 10:40, 41) ኢየሱስ ለሁሉም ሰው ያልተገለጠው ለምንድን ነው? የኢየሱስ ጠላቶች የሆኑት የሃይማኖት መሪዎች ከሞት መነሳቱን ሲሰሙ ይህ ዜና እንዳይሰራጭ ለማድረግ ሴራ እንደጠነሰሱ የማቴዎስ ዘገባ ይነግረናል።—ማቴዎስ 28:11-15

ታዲያ ኢየሱስ ትንሣኤው ሚስጥር ሆኖ እንዲቀር ይፈልግ ነበር ማለት ነው? በፍጹም፤ ምክንያቱም ጴጥሮስ በመቀጠል እንዲህ ብሏል፦ “አምላክ እሱን በሕያዋንና በሙታን ላይ ፈራጅ አድርጎ እንደሾመው ለሰዎች እንድንሰብክና በተሟላ ሁኔታ እንድንመሠክር አዘዘን።” እውነተኛ ክርስቲያኖች በዚያ ዘመን ይህን አድርገዋል፤ አሁንም እንዲህ እያደረጉ ነው።—የሐዋርያት ሥራ 10:42

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ