የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • km 9/03 ገጽ 1-3
  • ትሕትናን ልበሱ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ትሕትናን ልበሱ
  • የመንግሥት አገልግሎታችን—2003
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ትሕትናን መልበስ ያለብን ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1991
  • ይሖዋ ትሑት አገልጋዮቹን ከፍ አድርጎ ይመለከታል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2019
  • እውነተኛ ትሕትናን አዳብሩ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
  • “እኔ . . . በልቤ ትሑት ነኝ”
    “ተከታዬ ሁን”
ለተጨማሪ መረጃ
የመንግሥት አገልግሎታችን—2003
km 9/03 ገጽ 1-3

ትሕትናን ልበሱ

1 አንድ ልጅ እግር እረኛ በይሖዋ በመተማመን ኃያል የሆነን ጦረኛ አሸነፈ። (1 ሳ⁠ሙ. ​17:45-47) አንድ ባለጸጋ ሰው የደረሰበትን መከራ በጽናት ተቋቋመ። (ኢዮብ 1:​20-22፤ 2:9, 10) የአምላክ ልጅ ትምህርቱን ያገኘው ከአባቱ መሆኑን ተናገረ። (ዮሐ. 7:15-18፤ 8:28) በሦስቱም ሁኔታዎች ላይ ጎልቶ የሚታየው ባሕርይ ትሕትና ነው። ዛሬም በተመሳሳይ የሚያጋጥሙንን የተለያዩ ሁኔታዎች ለመወጣት ትሕትና በጣም ይረዳናል።​—⁠ቆላ. 3:12

2 በምንሰብክበት ጊዜ:- ክርስቲያን አገልጋዮች እንደመሆናችን መጠን በዘራቸው፣ በባህላቸው ወይም በአስተዳደጋቸው ምክንያት አድልዎ ሳናደርግ ለሁሉም ዓይነት ሰዎች ምሥራቹን በትሕትና እንሰብካለን። (1 ቆ⁠ሮ. 9:22, 23) አንዳንዶች ቢያመናጭቁን ወይም ለመንግሥቱ መልእክት ንቀት የተሞላበት ምላሽ ቢሰጡን አጸፋውን ከመመለስ ይልቅ የሚገባቸውን ሰዎች በትዕግሥት መፈለጋችንን እንቀጥላለን። (ማቴ. 10:11, 14) እኛ ከምናቀርበው ከማንኛውም ሐሳብ ይልቅ የአምላክ ቃል ይበልጥ አሳማኝ እንደሆነ በመገንዘብ የሰዎችን ትኩረት ወደ ቃሉ ለማዞር እንጥራለን እንጂ በእውቀታችን ወይም በትምህርታችን ልናስደምማቸው አንሞክርም። (1 ቆ⁠ሮ. 2:1-5፤ ዕብ. 4:12) የኢየሱስን ምሳሌ በመከተል ይሖዋ እንዲመሰገን እናደርጋለን።​—⁠ማር. 10:17, 18

3 በጉባኤ ውስጥ:- ክርስቲያኖች ‘እርስ በርሳቸው እየተዋረዱ ትሕትናን እንደ ልብስ መታጠቅ’ አለባቸው። (1 ጴ⁠ጥ. 5:5) ሌሎች ከእኛ እንደሚበልጡ አድርገን የምናስብ ከሆነ ወንድሞቻችን እንዲያገለግሉን ከመጠበቅ ይልቅ እነርሱን ማገልገል የምንችልባቸውን መንገዶች እንፈልጋለን። (ዮሐ. 13:12-17፤ ፊልጵ. 2:3, 4) የመሰብሰቢያ አዳራሹን ማጽዳትን የመሳሰሉ ሥራዎች ክብራችንን እንደሚነኩ አድርገን ማሰብ አይገባንም።

4 ትሕትና ‘እርስ በእርሳችን በፍቅር እንድንታገሥ’ ስለሚያስችለን በጉባኤ ውስጥ ሰላምና አንድነት ለማስፈን ይረዳል። (ኤፌ. 4:1-3) ለጉባኤው አመራር እንዲሰጡ ለተሾሙት ወንድሞች እንድንገዛ ይረዳናል። (ዕብ. 13:17) የሚሰጠንን ማንኛውንም ምክር ወይም ተግሣጽ እንድንቀበል ያነሳሳናል። (መዝ. 141:5) ከዚህም በላይ ትሕትና በጉባኤ ውስጥ የሚሰጠንን ማንኛውንም ኃላፊነት በመወጣት ረገድ በይሖዋ እንድንታመን ያደርገናል። (1 ጴ⁠ጥ. 4:11) እንደ ዳዊት እኛም ሊሳካልን የሚችለው በሰብዓዊ ችሎታ ሳይሆን በአምላክ እርዳታ መሆኑን እንገነዘባለን።​—⁠1 ሳ⁠ሙ. 17:37

5 በአምላካችን ፊት:- ከሁሉ በላይ ደግሞ ‘ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችንን ማዋረድ’ ይገባናል። (1 ጴ⁠ጥ. 5:6) አስቸጋሪ ከሆኑ ሁኔታዎች ጋር እየታገልን ከሆነ የአምላክ መንግሥት መጥቶ እንዲገላግለን እንናፍቅ ይሆናል። ሆኖም ይሖዋ የገባውን ቃል በወሰነው ጊዜ እስኪፈጽም ድረስ በትሕትና እንጠብቃለን። (ያዕ. 5:7-11) በአቋሙ እንደጸናው እንደ ኢዮብ ሁሉ እኛም በዋነኛነት የሚያሳስበን “የእግዚአብሔር ስም የተባረከ” መሆኑ ነው።​—⁠ኢዮብ 1:21

6 ነቢዩ ዳንኤል ‘ሰውነቱን በአምላኩ ፊት በማዋረዱ’ የይሖዋን ሞገስና ሌሎች ብዙ አስደሳች መብቶች በማግኘት ተባርኳል። (ዳን. 10:11, 12) በተመሳሳይ እኛም “ትሕትናና እግዚአብሔርን መፍራት ባለጠግነት ክብር ሕይወትም” እንደሆነ በመገንዘብ ትሕትናን እንልበስ።​—⁠ምሳሌ 22:4

[በገጽ 1 ላይ የሚገኝ የሥዕል መግለጫ]

(በገጽ 3 የመጀመሪያው አምድ ላይ ይቀጥላል )

[በገጽ 3 ላይ የሚገኝ የሥዕል መግለጫ]

ትህትናን ልበሱ

(ከገጽ 1 የዞረ )

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ