የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • wp20 ቁጥር 3 ገጽ 10
  • የፈጣሪን በረከት ለማግኘት አዘውትረህ ጸልይ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የፈጣሪን በረከት ለማግኘት አዘውትረህ ጸልይ
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2020
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በትሕትና እና ከልብህ ጸልይ
  • ወደ አምላክ ስትጸልይ በስሙ ተጠቀም
  • በቋንቋህ ጸልይ
  • በጸሎት አማካኝነት ከአምላክ ጋር ያለህን ዝምድና አጠናክር
    ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው?
  • ወደ አምላክ የመጸለይ ውድ መብት
    መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያስተምረናል?
  • በጸሎት አማካኝነት ወደ አምላክ ቅረብ
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
  • በጸሎት እርዳታ ማግኘት የሚቻለው እንዴት ነው?
    በምድር ላይ በገነት ለዘላለም መኖር ትችላለህ
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2020
wp20 ቁጥር 3 ገጽ 10
በመካከለኛው ምሥራቅ ያለ ሰው እየጸለየ።

“ጸሎት ሰሚ” የሆነው አምላክ የእኛን ጸሎት መስማት ያስደስተዋል።—መዝሙር 65:2

የፈጣሪን በረከት ለማግኘት አዘውትረህ ጸልይ

አምላክ ለሰው ልጆች ልዩ ስጦታ ሰጥቷቸዋል፤ ይህም ሐሳባቸውንና ስሜታቸውን በጸሎት ለእሱ የመግለጽ መብት ነው። ነቢዩ ዳዊት “ጸሎት ሰሚ የሆንከው አምላክ ሆይ፣ ሁሉም ዓይነት ሰው ወደ አንተ ይመጣል” በማለት ጸልዮአል። (መዝሙር 65:2) ይሁንና አምላክ ጸሎታችንን እንዲሰማንና እንዲባርከን ምን ዓይነት ጸሎት ማቅረብ ይኖርብናል?

በትሕትና እና ከልብህ ጸልይ

በግልህ ወደ አምላክ ስትጸልይ ልብህን በፊቱ ማፍሰስ ወይም የውስጥ ስሜትህን ለእሱ መንገር ትችላለህ። (መዝሙር 62:8) ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ ከልብህ የምታቀርበውን ጸሎት ከፍ አድርጎ ይመለከተዋል።

ወደ አምላክ ስትጸልይ በስሙ ተጠቀም

አምላክ ብዙ የማዕረግ ስሞች ቢኖሩትም የግል ስሙ አንድ ብቻ ነው። ፈጣሪያችን “እኔ ይሖዋ ነኝ። ስሜ ይህ ነው” ብሏል። (ኢሳይያስ 42:8) ይሖዋ የሚለው ስም በቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ወደ 7,000 ጊዜ ገደማ ይገኛል። በርካታ ነቢያት አምላክን የጠሩት በግል ስሙ ነው። አብርሃም “ይሖዋ እባክህ . . . አሁንም ልናገር” የሚል ጥያቄ አቅርቦ ነበር። (ዘፍጥረት 18:30) እኛም ስንጸልይ፣ ይሖዋ የተባለውን የአምላክ ስም መጠቀም ይኖርብናል።

በቋንቋህ ጸልይ

የምንጠቀምበት ቋንቋ ምንም ይሁን ምን፣ አምላክ ሐሳባችንን እና ስሜታችንን ይረዳል። ቃሉ የሚከተለውን ማረጋገጫ ይሰጠናል፦ “አምላክ [አያዳላም]፤ ከዚህ ይልቅ ከየትኛውም ብሔር ቢሆን እሱን የሚፈራና ትክክል የሆነውን ነገር የሚያደርግ ሰው በእሱ ዘንድ ተቀባይነት አለው።”—የሐዋርያት ሥራ 10:34, 35

ይሁን እንጂ የአምላክን በረከት ለማግኘት ከጸሎት በተጨማሪ ማድረግ የሚጠበቅብን ነገር አለ። ይህ ምን እንደሆነ በቀጣዮቹ ርዕሶች ላይ እንመለከታለን።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ