የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mwb18 ግንቦት ገጽ 4
  • እምነት የሚያጠናክር ራእይ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • እምነት የሚያጠናክር ራእይ
  • ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2018
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የክርስቶስ መለወጥ እንዴት እንደሚነካህ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—1991
  • በተአምራዊ ሁኔታ ተለወጠ—ክርስቶስ በክብሩ ታየ
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ትንቢት የሚያተኩረው በክርስቶስ ላይ ነው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2005
  • የአምላክን ትንቢታዊ ቃል በትኩረት ተከታተል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2000
ለተጨማሪ መረጃ
ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2018
mwb18 ግንቦት ገጽ 4

ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት | ማርቆስ 9-10

እምነት የሚያጠናክር ራእይ

9:1-7

ጴጥሮስ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ኢየሱስ በተአምር ሲለወጥ በራእይ ሲመለከቱ

ኢየሱስ ተአምራዊ በሆነ መንገድ በተለወጠበት ወቅት በሰማይ ያለው አባቱ በእሱ ደስ እንደሚሰኝ ሲናገር መስማቱ እምነቱን በእጅጉ አጠናክሮለት እንደሚሆን መገመት አያዳግትም። ይህን መስማቱ ከፊቱ የሚጠብቀውን መከራ በድፍረት ለመጋፈጥ የሚያስችል ጥንካሬ እንደሰጠው ምንም ጥርጥር የለውም። ራእዩ በጴጥሮስ፣ በያዕቆብና በዮሐንስም ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል። ኢየሱስ በእርግጥ መሲሕ እንደሆነና እሱን መስማታቸው ተገቢ እንደሆነ አረጋግጦላቸዋል። ጴጥሮስ ከ32 ዓመት በኋላ እንኳ በዚያ ወቅት የተከሰተውን ነገር እንዲሁም ይህ ሁኔታ ‘በትንቢታዊው ቃል’ ላይ ያለውን እምነት ምን ያህል እንዳጠናከረለት አስታውሶ ተናግሯል።—2ጴጥ 1:16-19

እኛ ይህን አስደናቂ ራእይ በገዛ ዓይናችን ባናይም እንኳ ፍጻሜውን ሲያገኝ እየተመለከትን ነው። ኢየሱስ ኃያል ንጉሥ ሆኖ እየገዛ ነው። በቅርቡ ደግሞ ‘ድሉን በማጠናቀቅ’ ጽድቅ ወደሰፈነበት አዲስ ዓለም እንድንገባ ያደርገናል።—ራእይ 6:2

የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ሲፈጸሙ ማየትህ እምነትህን ያጠናከረልህ እንዴት ነው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ