የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mwb19 ጥቅምት ገጽ 8
  • ይሖዋ ንጹሕ ሰዎችን ይወዳል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ይሖዋ ንጹሕ ሰዎችን ይወዳል
  • ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2019
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ንጽሕና—ትክክለኛ ትርጉሙ ምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • ንጽሕና ምን ያህል አስፈላጊ ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • አምላክ ንጹሕ የሆኑ ሰዎችን ይወዳል
    ‘ከአምላክ ፍቅር አትውጡ’
  • ንጽሕና አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2008
ለተጨማሪ መረጃ
ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2019
mwb19 ጥቅምት ገጽ 8
አንድ ወንድም የስብሰባ አዳራሹን መጸዳጃ ቤት ሲያጸዳ

ክርስቲያናዊ ሕይወት

ይሖዋ ንጹሕ ሰዎችን ይወዳል

ብዙ ወላጆች “እጅህን ታጠብ፤ ክፍልህን አጽዳ፤ መሬቱን ጥረግ፤ ቆሻሻውን ድፋ” እንደሚሉት ያሉ መመሪያዎችን በመስጠት ልጆቻቸው ንጽሕናቸውን እንዲጠብቁ ያስተምራሉ። ይሁንና እነዚህ የንጽሕና መሥፈርቶች የመነጩት ቅዱስ ከሆነው አምላካችን ነው። (ዘፀ 30:18-20፤ ዘዳ 23:14፤ 2ቆሮ 7:1) ሰውነታችንንም ሆነ ንብረታችንን በንጽሕና ስንይዝ ይሖዋን እናስከብራለን። (1ጴጥ 1:14-16) ቤታችንንና አካባቢያችንን በተመለከተስ ምን ማለት ይቻላል? በየመንገዱና በየመናፈሻው ቆሻሻ ከሚጥሉ ሰዎች በተለየ እኛ ክርስቲያኖች መኖሪያችን የሆነችውን ምድርን ላለማቆሸሽ እንጠነቀቃለን። (መዝ 115:16፤ ራእይ 11:18) የከረሜላ ልጣጭ፣ የውኃ መያዣ ፕላስቲክ ወይም ማስቲካ እንደምንጥልበት መንገድ ያሉ ትናንሽ ነገሮች እንኳ ለንጽሕና ያለንን አመለካከት ያሳያሉ። በሁሉም የሕይወታችን ዘርፎች “ራሳችንን ብቁ የአምላክ አገልጋዮች አድርገን” ማቅረብ እንፈልጋለን።—2ቆሮ 6:3, 4

አምላክ ንጹሕ ሰዎችን ይወዳል የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦

  • አንዳንዶች ንብረታቸውን በንጽሕና ላለመያዝ ምን ሰበብ ሊያቀርቡ ይችላሉ?

  • የሙሴ ሕግ ይሖዋ ለንጽሕና ያለውን አመለካከት የሚያሳየው እንዴት ነው?

  • ምንም ነገር መናገር ሳያስፈልገን ስለ ይሖዋ መመሥከር የምንችለው እንዴት ነው?

አንድ አባት የልጁ የቆሸሸ መኪና ውስጥ ሲገባ፤ አባትየውና ልጁ ይሖዋ ስለ ንጽሕና ያለውን መሥፈርት በተመለከተ ሲነጋገሩ፤ በጥንቷ እስራኤል ሁለት ካህናት ለመታጠቢያ በሚያገለግለው የመዳብ ገንዳ አጠገብ ሆነው፤ አብረው የሚያገለግሉ ወንድሞች ከልጁ ንጹሕ መኪና ሲወጡ

ይሖዋ ለንጽሕና ያለውን አመለካከት በግል ሕይወቴ ማንጸባረቅ የምችለው እንዴት ነው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ