የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • mwb23 ጥር ገጽ 9
  • ይሖዋ ፈተናዎችን እንድንወጣ ይረዳናል

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ይሖዋ ፈተናዎችን እንድንወጣ ይረዳናል
  • ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2023
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ይሖዋ “ሕያው አምላክ” እንደሆነ አስታውስ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2024
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017
  • መቼም ቢሆን ብቻችንን አይደለንም
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
  • ይሖዋ እንድንጸና የሚረዳን እንዴት ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2025
ለተጨማሪ መረጃ
ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን​—የስብሰባው አስተዋጽኦ—2023
mwb23 ጥር ገጽ 9
ወላጆችና ሁለት ትናንሽ ልጆቻቸው በቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካኝነት ከጉባኤያቸው ጋር ሲጨዋወቱ።

ክርስቲያናዊ ሕይወት

ይሖዋ ፈተናዎችን እንድንወጣ ይረዳናል

በእነዚህ የመጨረሻ ቀናት በርካታ ከባባድ ፈተናዎች ያጋጥሙናል። አንዳንድ ጊዜ ያጋጠሙን ፈተናዎች ከአቅማችን በላይ እንደሆኑ ይሰማን ይሆናል። ይሁንና ወደ ይሖዋ መቅረባችንን ከቀጠልን እሱ ቅስም የሚሰብሩ ፈተናዎችን እንኳ እንድንወጣ ይረዳናል። (ኢሳ 43:2, 4) ታዲያ በፈተና ውስጥ ሆነንም ወደ ይሖዋ መቅረብ የምንችለው እንዴት ነው?

ጸሎት። ልባችንን በይሖዋ ፊት ስናፈስ እሱ ለመጽናት የሚያስችል የአእምሮ ሰላምና የመንፈስ ጥንካሬ ይሰጠናል።—ፊልጵ 4:6, 7፤ 1ተሰ 5:17

ስብሰባ። ይሖዋ በስብሰባዎች አማካኝነት የሚሰጠን መንፈሳዊ ምግብና ከወንድሞቻችን የምናገኘው ማበረታቻ ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ ያስፈልገናል። (ዕብ 10:24, 25) ለስብሰባዎች ስንዘጋጅ፣ በስብሰባዎች ላይ ስንገኝ እንዲሁም ሐሳብ ስንሰጥ ይሖዋ በመንፈሱ አማካኝነት ከሚሰጠው እርዳታ ሙሉ ጥቅም ማግኘት እንችላለን።—ራእይ 2:29

አገልግሎት። አቅማችን በፈቀደ መጠን በአገልግሎት ላይ የተሟላ ተሳትፎ ስናደርግ አዎንታዊ በሆኑ ነገሮች ላይ ማተኮር ይበልጥ ቀላል ይሆንልናል። ከዚህም ሌላ፣ ከይሖዋና አብረውን ከሚሠሩት ሰዎች ጋር ያለን ወዳጅነት እየተጠናከረ ይሄዳል።—1ቆሮ 3:5-10

ይሖዋ ይቀበላችኋል የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦

  • ማሉ ፈተና ባጋጠማት ወቅት ወደ ይሖዋ እንድትቀርብ የረዳት ምንድን ነው?

  • ልክ እንደ ማሉ በመዝሙር 34:18 ላይ የሚገኘው ሐሳብ በፈተና ወቅት የሚያጽናናን እንዴት ነው?

  • የማሉ ተሞክሮ ይሖዋ በፈተና ወቅት ‘ከሰብዓዊ ኃይል በላይ የሆነውን ኃይል’ እንደሚሰጠን የሚያሳየው እንዴት ነው?—2ቆሮ 4:7

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ