የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w20 ግንቦት ገጽ 8-11
  • በፍጻሜው ዘመን የተነሱ ተቀናቃኝ ነገሥታት

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • በፍጻሜው ዘመን የተነሱ ተቀናቃኝ ነገሥታት
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ‘የሰሜኑ ንጉሥ’ በፍጻሜው ዘመን
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • ይሖዋ “በቅርብ ጊዜ ውስጥ ሊፈጸሙ የሚገባቸውን ነገሮች” ይገልጣል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2012
  • በዛሬው ጊዜ ‘የሰሜኑ ንጉሥ’ ማን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • አንድ አስገራሚ ምሥጢር ተፈታ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
w20 ግንቦት ገጽ 8-11

በፍጻሜው ዘመን የተነሱ ተቀናቃኝ ነገሥታት

በዚህ ሰንጠረዥ ላይ የተጠቀሱ አንዳንድ ትንቢቶች ፍጻሜያቸውን ያገኙት በተመሳሳይ ጊዜ ላይ ነው። ትንቢቶቹ በሙሉ፣ የምንኖረው ‘በፍጻሜው ዘመን’ እንደሆነ በተለያየ መንገድ ያረጋግጣሉ።—ዳን. 12:4

የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶችን እንዲሁም ከ1870 እስከ ዛሬ ድረስ የተነሱ የሰሜን እና የደቡብ ነገሥታትን ማንነት የሚያሳይ ሰንጠረዥ።
  • ሰንጠረዥ 1፦ ከ1870 እስከ 1918 ባሉት ዓመታት በተመሳሳይ ጊዜ የተፈጸሙ የፍጻሜው ዘመን ትንቢቶች። ከ1914 ወዲህ ያሉት ዓመታት የፍጻሜው ዘመን ተብሎ የሚጠራው ጊዜ ክፍል ናቸው። ትንቢት 1፦ በጊዜ ሰሌዳው መጀመሪያ ላይ ሰባት ራስ ያለው አውሬ ይታያል። በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የአውሬው ሰባተኛ ራስ ቆሰለ። ከ1917 በኋላ ሰባተኛው ራስ የዳነ ከመሆኑም ሌላ አውሬው ከጉዳቱ አገገመ። ትንቢት 2፦ በ1871 የሰሜኑ ንጉሥ ማንነት ግልጽ ሆነ፤ በ1870 የደቡቡ ንጉሥ ማንነት ግልጽ ሆነ። በ1871 የጀርመን መንግሥት የሰሜኑ ንጉሥ ሆኖ ብቅ አለ። በዚህ ወቅት የደቡቡ ንጉሥ ሆኖ ብቅ ያለው የታላቋ ብሪታንያ መንግሥት ነው፤ በኋላ ላይ ማለትም በ1917 ግን የአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃይል መንግሥት የደቡቡ ንጉሥ ሆነ። ትንቢት 3፦ ከ1870ዎቹ ዓመታት አንስቶ ቻርልስ ቴዝ ራስል እና አጋሮቹ በትንቢት የተነገረለት “መልእክተኛ” ሆነዋል። በ1880ዎቹ መጀመሪያ ላይ ‘የጽዮን መጠበቂያ ግንብ’ አንባቢዎቹ ምሥራቹን እንዲሰብኩ አበረታታ። ትንቢት 4፦ ከ1914 ወዲህ የመከር ወቅት ተጀመረ። ስንዴው ከእንክርዳዱ ተለየ። ትንቢት 5፦ ከ1917 አንስቶ የብረቱ እና የሸክላው እግር ብቅ አለ። ከእነዚህ በተጨማሪ በሰንጠረዡ ላይ የሚታዩት ነገሮች፦ ከ1914 እስከ 1918 በዓለም ላይ የተከሰቱ ነገሮች፦ አንደኛው የዓለም ጦርነት። የይሖዋን ሕዝቦች የነኩ ክንውኖች፦ ከ1914 እስከ 1918 ባሉት ዓመታት በብሪታንያ እና በጀርመን የሚገኙ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ታስረዋል። በ1918 በዩናይትድ ስቴትስ የሚገኘው ዋና መሥሪያ ቤት አባላት ታሰሩ።
    ትንቢት 1።

    ጥቅስ፦ ራእይ 11:7፤ 12:13, 17፤ 13:1-8, 12

    ትንቢት፦ “አውሬው” የምድርን ነዋሪዎች ለበርካታ መቶ ዘመናት ይገዛል። በፍጻሜው ዘመን የአውሬው ሰባተኛ ራስ ይቆስላል። በኋላ ላይ ይህ ራስ ቁስሉ ይድንለታል፤ “ምድርም ሁሉ” አውሬውን ይከተለዋል። ሰይጣን ይህን አውሬ በመጠቀም ‘ቀሪዎቹን ይዋጋል።’

    ፍጻሜ፦ ከጥፋት ውኃ በኋላ ይሖዋን የሚቃወሙ ሰብዓዊ መንግሥታት ተነስተዋል። ከብዙ መቶ ዘመናት በኋላ፣ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የብሪታንያ መንግሥት በእጅጉ ተዳክሞ ነበር። ሆኖም ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ጥምረት ሲፈጥር ማንሰራራት ቻለ። በተለይ በፍጻሜው ዘመን ሰይጣን በእሱ ቁጥጥር ሥር ያለውን የፖለቲካ ሥርዓት ተጠቅሞ የአምላክን ሕዝቦች ያሳድዳል።

  • ትንቢት 2።

    ጥቅስ፦ ዳን. 11:25-45

    ትንቢት፦ በፍጻሜው ዘመን በሰሜኑ ንጉሥና በደቡቡ ንጉሥ መካከል የሚኖረው ሽኩቻ።

    ፍጻሜ፦ የጀርመን መንግሥትና የአንግሎ አሜሪካ ጥምር ኃይል ተቀናቃኝ ሆኑ። በ1945 ሶቪየት ኅብረት እና አጋሮቹ የሰሜኑ ንጉሥ ሆኑ። በ1991 ሶቪየት ኅብረት ፈራረሰ፤ ከጊዜ በኋላ ሩሲያና አጋሮቿ የሰሜኑ ንጉሥ ሆኑ።

  • ትንቢት 3።

    ጥቅስ፦ ኢሳ. 61:1፤ ሚል. 3:1፤ ሉቃስ 4:18

    ትንቢት፦ ይሖዋ፣ መሲሐዊው መንግሥት ከመቋቋሙ በፊት ‘መንገድ የሚጠርግ መልእክተኛ’ ይልካል። “መልእክተኛ” የሚሆነው ቡድን “የዋህ ለሆኑ ሰዎች ምሥራች” ይናገራል።

    ፍጻሜ፦ ከ1870ዎቹ ዓመታት አንስቶ ቻርልስ ቴዝ ራስል እና አጋሮቹ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችን ለማብራራት ትጋት የተሞላበት ጥረት አድርገዋል። በ1880ዎቹ ዓመታት ደግሞ የአምላክ አገልጋዮች መስበክ እንዳለባቸው ጎላ አድርገው መግለጽ ጀመሩ። ካወጧቸው ርዕሶች መካከል “1,000 ሰባኪዎች ያስፈልጋሉ” እና “ለስብከት መቀባት” የሚሉት ይገኙበታል።

  • ትንቢት 4።

    ጥቅስ፦ ማቴ. 13:24-30, 36-43

    ትንቢት፦ አንድ ጠላት በስንዴ ማሳ ላይ እንክርዳድ ይዘራል፤ እስከ መከር ወቅት ድረስ እንክርዳዱ ከስንዴው ጋር እንዲያድግ ይተዋል፤ ስንዴውም በእንክርዳዱ ይዋጣል፤ ከዚያም እንክርዳዱን ከስንዴው የመለየቱ ሥራ ይከናወናል።

    ፍጻሜ፦ ከ1800ዎቹ ዓመታት መገባደጃ አንስቶ በእውነተኛ ክርስቲያኖችና በሐሰተኛ ክርስቲያኖች መካከል ያለው ልዩነት ይበልጥ ግልጽ እየሆነ መጣ። በፍጻሜው ዘመን እውነተኛ ክርስቲያኖች ይሰበሰባሉ፤ እንዲሁም ከሐሰተኛ ክርስቲያኖች ይለያሉ።

  • ትንቢት 5።

    ጥቅስ፦ ዳን. 2:31-33, 41-43

    ትንቢት፦ የብረትና የሸክላ እግር፤ ይህ እግር ከተለያዩ የብረት ዓይነቶች የተሠራው ምስል ክፍል ነው።

    ፍጻሜ፦ ሸክላው፣ በአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃያል መንግሥት ግዛት ውስጥ የሚደረጉ ሕዝባዊ ንቅናቄዎችን ያመለክታል። እነዚህ ንቅናቄዎች ይህ የዓለም ኃያል መንግሥት እንደ ብረት ያለ ጥንካሬውን እንዳይጠቀምበት ያዳክሙታል።

  • ሰንጠረዥ 2፦ ከ1919 እስከ 1945 በተመሳሳይ ጊዜ የተፈጸሙ የፍጻሜው ዘመን ትንቢቶች። የጀርመን መንግሥት እስከ 1945 ድረስ የሰሜኑ ንጉሥ ሆኖ ቀጥሏል። የደቡቡ ንጉሥ፣ የአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃያል መንግሥት ነው። ትንቢት 6፦ በ1919 ቅቡዓን ክርስቲያኖች ወደነጻው ጉባኤ ተሰበሰቡ። ከ1919 አንስቶ የስብከቱ ሥራ ተጠናክሮ ቀጠለ። ትንቢት 7፦ በ1920 የመንግሥታት ቃል ኪዳን ማኅበር ተቋቋመ፤ ይህ ድርጅት ሁለተኛው የዓለም ጦርነት እስከጀመረበት ጊዜ ድረስ ቀጥሏል። ከእነዚህ በተጨማሪ በሰንጠረዡ ላይ የሚታዩት ነገሮች፦ ትንቢት 1፦ ሰባት ራስ ያለው አውሬ ይቀጥላል። ትንቢት 5፣ የብረቱና የሸክላው እግር ይቀጥላል። ከ1939 እስከ 1945 በዓለም ላይ የተከሰቱ ነገሮች፦ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት። የይሖዋን ሕዝቦች የነኩ ክንውኖች፦ ከ1933 እስከ 1945፣ በጀርመን የሚገኙ ከ11,000 የሚበልጡ የይሖዋ ምሥክሮች ታስረዋል። ከ1939 እስከ 1945 በብሪታንያ የሚገኙ 1,600 ገደማ የሚሆኑ የይሖዋ ምሥክሮች ታሰሩ። ከ1940 እስከ 1944 በዩናይትድ ስቴትስ የሚገኙ የይሖዋ ምሥክሮች ከ2,500 ጊዜ በላይ የሕዝብ ዓመፅ ገጥሟቸዋል።
    ትንቢት 6።

    ጥቅስ፦ ማቴ. 13:30፤ 24:14, 45፤ 28:19, 20

    ትንቢት፦ “ስንዴው” ወደ “ጎተራ” ይሰበሰባል፤ እንዲሁም “ታማኝና ልባም ባሪያ” “በቤተሰቦቹ” ላይ ይሾማል። “የመንግሥቱ ምሥራች . . . በመላው ምድር” መሰበክ ይጀምራል።

    ፍጻሜ፦ በ1919 ታማኙ ባሪያ በአምላክ ሕዝቦች ላይ ተሾመ። ከዚያ ጊዜ አንስቶ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች የስብከቱን ሥራ አጧጧፉት። በዛሬው ጊዜ የይሖዋ ምሥክሮች ከ200 በሚበልጡ አገሮች ውስጥ እየሰበኩ ነው፤ እንዲሁም ከ1,000 በሚበልጡ ቋንቋዎች መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጽሑፎችን ያዘጋጃሉ።

  • ትንቢት 7።

    ጥቅስ፦ ዳን. 12:11፤ ራእይ 13:11, 14, 15

    ትንቢት፦ ባለ ሁለት ቀንዱ አውሬ፣ ‘ለአውሬው ምስል እንዲሠራ’ ትእዛዝ ያስተላልፋል፤ ‘ለምስሉም እስትንፋስ ይሰጠዋል።’

    ፍጻሜ፦ የአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃያል መንግሥት፣ ቅድሚያውን ወስዶ የመንግሥታት ቃል ኪዳን ማኅበር የተባለ ድርጅት እንዲቋቋም አድርጓል። ሌሎች አገራትም ይህን ድርጅት ተቀላቅለዋል። ከጊዜ በኋላ የሰሜኑ ንጉሥም ይህን ማኅበር ተቀላቅሏል፤ ሆኖም ኅብረት ፈጥሮ የቆየው ከ1926 እስከ 1933 ብቻ ነበር። በኋላ ላይ እንደተቋቋመው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሁሉ ይህ ማኅበርም ለአምላክ መንግሥት ብቻ የሚገባው እውቅና ተሰጥቶታል።

  • ሰንጠረዥ 3፦ ከ1945 እስከ 1991 በተመሳሳይ ጊዜ የተፈጸሙ የፍጻሜው ዘመን ትንቢቶች። እስከ 1991 ድረስ የሰሜኑ ንጉሥ የሆኑት ሶቪየት ኅብረትና አጋሮቿ ናቸው፤ በኋላም ሩሲያ እና አጋሮቿ ይህን ቦታ ያዙ። የደቡቡ ንጉሥ፣ የአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃያል መንግሥት ነው። ትንቢት 8፦ አቶሚክ ፍንዳታ የፈጠረው ደመና፤ የአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃያል መንግሥት ያስከተለውን ውድመት የሚያሳይ ነው። ትንቢት 9፦ በ1945 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተቋቋመ፤ ይህ ድርጅት የመንግሥታት ቃል ኪዳን ማኅበርን የሚተካ ነበር። ከእነዚህ በተጨማሪ በሰንጠረዡ ላይ የሚታዩት ነገሮች፦ ትንቢት 1፦ ሰባት ራስ ያለው አውሬ ይቀጥላል። ትንቢት 5፦ የብረቱና የሸክላው እግር ይቀጥላል። ትንቢት 6፦ በ1945 ከ156,000 የሚበልጡ አስፋፊዎች ነበሩ። በ1991 ከ4,278,000 የሚበልጡ አስፋፊዎች ነበሩ። የይሖዋን ሕዝቦች የነኩ ክንውኖች፦ ከ1945 እስከ 1950ዎቹ ባሉት ዓመታት፣ በሶቪየት ኅብረት የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ የይሖዋ ምሥክሮች ወደ ሳይቤሪያ ተግዘዋል።
    ትንቢት 8።

    ጥቅስ፦ ዳን. 8:23, 24

    ትንቢት፦ አስፈሪ መልክ ያለው ንጉሥ “ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ጥፋት ያደርሳል።”

    ፍጻሜ፦ የአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃያል መንግሥት ብዙ ጥፋት አድርሷል። ለምሳሌ ያህል፣ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት፣ የአንግሎ አሜሪካ ጥምር ኃይል ጠላት በሆነ አገር ላይ ሁለት አቶሚክ ቦምቦች ጥሏል፤ ይህም ታይቶ የማይታወቅ አስከፊ ጥፋት አስከትሏል።

  • ትንቢት 9።

    ጥቅስ፦ ዳን. 11:31፤ ራእይ 17:3, 7-11

    ትንቢት፦ አሥር ቀንዶች ያሉት “ደማቅ ቀይ” አውሬ ከጥልቁ ይወጣል፤ ስምንተኛ ንጉሥም ይሆናል። ይህ ንጉሥ፣ በዳንኤል መጽሐፍ ላይ ‘ጥፋት የሚያመጣው ርኩስ ነገር’ ተብሎ ተጠርቷል።

    ፍጻሜ፦ የመንግሥታት ቃል ኪዳን ማኅበር፣ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ከእንቅስቃሴ ውጭ ሆኖ ነበር። ከጦርነቱ በኋላ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተቋቋመ። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ ከእሱ በፊት እንደነበረው የቃል ኪዳኑ ማኅበር ሁሉ ለአምላክ መንግሥት የሚገባው ክብር ተሰጥቶታል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በሃይማኖት ላይ ጥቃት ይሰነዝራል።

  • ሰንጠረዥ 4፦ ከአሁኑ ጊዜ አንስቶ እስከ አርማጌዶን በተመሳሳይ ጊዜ የሚፈጸሙ የፍጻሜው ዘመን ትንቢቶች። የሰሜኑ ንጉሥ የሆኑት ሩሲያ እና አጋሮቿ ናቸው። የደቡቡ ንጉሥ፣ የአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃያል መንግሥት ነው። ትንቢት 10፦ የዓለም መንግሥታት ‘ሰላምና ደህንነት ሆነ’ ብለው ያውጃሉ። ከዚያም ታላቁ መከራ ይጀምራል። ትንቢት 11፦ ብሔራት በሐሰት ሃይማኖት ተቋማት ላይ ጥቃት ይሰነዝራሉ። ትንቢት 12፦ የዓለም መንግሥታት በአምላክ ሕዝቦች ላይ ጥቃት ይሰነዝራሉ። የቀሩት ቅቡዓን ወደ ሰማይ ይሰበሰባሉ። ትንቢት 13፦ አርማጌዶን። በነጭ ፈረስ ላይ የተቀመጠው፣ ድሉን ያጠናቅቃል። ሰባት ራስ ያለው አውሬ ይጠፋል፤ ግዙፉ ምስል፣ የብረትና የሸክላ ድብልቅ በሆነው እግሩ ላይ ተመትቶ ይደቅቃል። ከእነዚህ በተጨማሪ በሰንጠረዡ ላይ የሚታዩት ነገሮች፦ ትንቢት 1፦ ሰባት ራስ ያለው አውሬ እስከ አርማጌዶን ይቀጥላል። ትንቢት 5፣ የብረቱና የሸክላው እግር እስከ አርማጌዶን ይቀጥላል። ትንቢት 6፦ በዛሬው ጊዜ ከ8,580,000 የሚበልጡ አስፋፊዎች አሉ። የይሖዋን ሕዝቦች የነኩ ክንውኖች፦ በ2017 የሩሲያ ባለሥልጣናት የይሖዋ ምሥክሮችን አስረዋል እንዲሁም የቅርንጫፍ ቢሮውን ሕንፃዎች ወርሰዋል።
    ትንቢት 10 እና 11።

    ጥቅስ፦ 1 ተሰ. 5:3፤ ራእይ 17:16

    ትንቢት፦ ብሔራት “ሰላምና ደህንነት ሆነ!” ብለው ያውጃሉ፤ “አሥሩ ቀንዶች” እና “አውሬው” “አመንዝራዋን” ያጠቋታል እንዲሁም ያጠፏታል። ከዚያም በብሔራት ላይ ጥፋት ይመጣል።

    ፍጻሜ፦ ብሔራት፣ ሰላም እና ደህንነት ማስፈን እንደቻሉ ይናገራሉ። ከዚያም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል የሆኑ ብሔራት፣ የሐሰት ሃይማኖት ተቋማትን ያጠፋሉ። ይህም ታላቁ መከራ እንደጀመረ የሚያሳይ ምልክት ይሆናል። ይህ መከራ የሚያበቃው መላው የሰይጣን ሥርዓት በአርማጌዶን ሲደመሰስ ነው።

  • ትንቢት 12።

    ጥቅስ፦ ሕዝ. 38:11, 14-17፤ ማቴ. 24:31

    ትንቢት፦ ጎግ የአምላክን ሕዝቦች ምድር ይወርራል። ከዚያም መላእክት “የተመረጡትን” ይሰበስባሉ።

    ፍጻሜ፦ የሰሜኑ ንጉሥ ከሌሎቹ የዓለም መንግሥታት ጋር በመሆን በአምላክ ሕዝቦች ላይ ጥቃት ይሰነዝራል። ይህ ጥቃት ከጀመረ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ፣ የቀሩት ቅቡዓን ወደ ሰማይ ይሰበሰባሉ።

  • ትንቢት 13።

    ጥቅስ፦ ሕዝ. 38:18-23፤ ዳን. 2:34, 35, 44, 45፤ ራእይ 6:2፤ 16:14, 16፤ 17:14፤ 19:20

    ትንቢት፦ ‘በነጭ ፈረስ’ ላይ “የተቀመጠው” ጋላቢ፣ ጎግንና ሠራዊቱን በማጥፋት ‘ድሉን ያጠናቅቃል።’ “አውሬው” ‘ወደ እሳት ሐይቅ ይወረወራል’፤ ትልቁ ምስልም ይደቅቃል።

    ፍጻሜ፦ የአምላክ መንግሥት ንጉሥ የሆነው ኢየሱስ የአምላክ ሕዝቦችን ይታደጋል። ከ144,000 ተባባሪ ገዢዎችና ከመላእክት ሠራዊት ጋር በመሆን ኢየሱስ፣ ጥምረት የፈጠሩ ብሔራትን ያጠፋል፤ መላው የሰይጣን ሥርዓት በዚህ መንገድ ይጠፋል።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ