ተጨማሪ ሐሳብ
^ [1] (አንቀጽ 16) “የአደባባይ ምሥክርነት” የሚለው አገላለጽ በአብዛኛው የሚያመለክተው ከቤት ወደ ቤት ከምናደርገው አገልግሎት ውጭ ያሉትን የስብከት ዘዴዎች ይኸውም በመኪና ማቆሚያዎች፣ በንግድ አካባቢዎች፣ በመናፈሻዎች፣ በመንገድ ላይና ሰዎች ሊገኙባቸው በሚችሉ ሌሎች ቦታዎች የምናከናውነውን ስብከት ነው። ሕዝብ በሚበዛባቸው አካባቢዎች ጋሪዎችን፣ ጠረጴዛዎችንና የመሳሰሉትን ተጠቅመን የምናከናውነው አገልግሎት የአደባባይ ምሥክርነት አንዱ ዘርፍ ነው።