የግርጌ ማስታወሻ
a የደም ግፊት በሚሊ ሜትር የሚለካ ሲሆን በመለኪያ መሣሪያው ውስጥ ያለው ሜርኩሪ ወደ ላይ ከፍ እንዲል ያደርጋል። ልብ ስትመታና ዘና ስትል የሚፈጠሩት የላእላይና የታህታይ ግፊቶች ሲስቶሊክ እና ዳያስቶሊክ ግፊቶች በመባል ይታወቃሉ። ይህ በዕድሜ፣ በጾታ፣ በአእምሯዊና በአካላዊ ውጥረት እንዲሁም በድካም የተነሳ ከሰው ወደ ሰው ሊለያይ ይችላል። ብዙውን ጊዜ የሴቶች የደም ግፊት ከወንዶቹ ዝቅ ያለ ነው። የልጆች የደም ግፊትም ዝቅ ያለ ሲሆን የአረጋውያን ግን ከፍ ያለ ነው። ምንም እንኳ በዚህ ጉዳይ ላይ ያሉት አመለካከቶች በመጠኑ ሊለያዩ ቢችሉም አንድ ጤናማ ወጣት ከ100 እስከ 140 ሚሊ ሜትር ሜርኩሪ ሲስቶሊክ እና ከ60 እስከ 90 ሚሊ ሜትር ዳያስቶሊክ የደም ግፊት ሊኖረው ይችላል።