የግርጌ ማስታወሻ
a ይህ ሐሳብ በአብዛኛው የተመሠረተው በ19ኛው መቶ ዘመን የኖረው ቪልፍሬዶ ፓሬቶ የተባለ ጣሊያናዊ ኢኮኖሚስት ባወጣው ደንብ ላይ ነው፤ ይህ ደንብ የፓሬቶ መመሪያ ተብሎም ይጠራል። ይህ ደንብ አንድን ሥራ ስናከናውን 20 በመቶ ለሚያህለው የሥራው ክፍል ትኩረት በመስጠት አብዛኛውን ጊዜ 80 በመቶ የሚሆን ውጤት ማግኘት እንደሚቻል የሚገልጸውን ሐሳብ የያዘ ነው። ደንቡ ለብዙ ነገሮች ይሠራል፤ ቀለል ባለ ምሳሌ ለማስረዳት ያህል፣ አንድን ምንጣፍ በአቧራ ማንሻ ማሽን ስናጸዳ እግር የሚበዛበትን 20 በመቶ የሚሆነውን የምንጣፉን ክፍል በማጽዳት ብቻ 80 በመቶ የሚሆነውን ቁሻሻ ማንሳት እንችላለን።