የግርጌ ማስታወሻ
c የሥላሴ ጽንሰ ሐሳብ የመጣው ከጥንትዋ ባቢሎን ነው። በዚያ አገር የፀሐይ አምላክ የሆነው ሻማሽ፣ የጨረቃ አምላክ የሆነው ሲንና የኮከብ አምላክ የሆነው ኢሽታር በሥላሴነት ይመለኩ ነበር። ግብፅም ይህንኑ የሚመስል የአምልኮ ሥርዓት በመከተል ኦሲሪስን፣ አይሲስንና ሆረስን ታመልክ ነበር። የአሶር ዋነኛ አምላክ የነበረው አሱር ሦስት ራሶች እንዳሉት ሆኖ ተስሎአል። የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንም ይህንኑ ሥርዓት በመከተል በየአብያተ ክርስቲያናትዋ አምላክ ሦስት ራሶች እንዳሉት ሆኖ እንዲሳል አድርጋለች።