የግርጌ ማስታወሻ
a ለምሳሌ ያህል፣ በናይጄሪያ የሚኖሩት የዮሩባ ጎሣ አባላት ነፍስ ሌላ ሥጋ ለብሳ ትመለሳለች የሚል ባሕላዊ እምነት አላቸው። በዚህም ምክንያት አንዲት እናት ልጅ ሲሞትባት የመረረ ሐዘን የሚሰማት ለአጭር ጊዜ ብቻ ነው። “ውኃው ተደፋ እንጂ ቅሉ አልተሰበረም” የሚል የተለመደ የዮሩባዎች አባባል አለ። በዮሩባዎች እምነት መሠረት፣ የውኃ መያዣ የሆነው ቅል ማለትም እናቲቱ ሌላ ልጅ ልትወልድ (ምናልባትም የሞተውን ልጅ በሌላ አካል እንደገና ልትወልደው) ትችላለች። የይሖዋ ምሥክሮች፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት የሌላቸውን ‘ነፍስ አትሞትም’ ወይም ‘ነፍስ ሌላ አካል ለብሳ ትመለሳለች’ ከሚሉ የተሳሳቱ አስተሳሰቦች የመነጩትን ወጎችና አጉል እምነቶች አይከተሉም።—መክብብ 9:5, 10፤ ሕዝቅኤል 18:4, 20