የግርጌ ማስታወሻ
a ኢሳይያስ በስም የጠቀሰው ሜዶንን ብቻ ነው። ይሁን እንጂ በባቢሎን ላይ አብረው የሚነሱት ነገሥታት በርከት ያሉ ሲሆኑ እነርሱም ሜዶን፣ ፋርስ፣ ኤላም እና ሌሎችም ትናንሽ ብሔራት ናቸው። (ኤርምያስ 50:9፤ 51:24, 27, 28) በአካባቢው የነበሩት አገሮች ሜዶንንና ፋርስን የሚጠሯቸው “ሜዶን” ብለው ነበር። ደግሞም በኢሳይያስ ዘመን ገናና ኃይል የነበረችው ሜዶን ናት። ፋርስ ኃያል ሆና ብቅ ያለችው በቂሮስ የግዛት ዘመን ነው።