የግርጌ ማስታወሻ
a የፋርሱ ንጉሥ ቂሮስ “የአንሻን ንጉሥ” እየተባለ የሚጠራበት ጊዜ ነበር። አንሻን ደግሞ በኤላም ውስጥ የምትገኝ አውራጃ ወይም ከተማ ነበረች። በኢሳይያስ ዘመን ማለትም በስምንተኛው መቶ ዘመን ከዘአበ የነበሩት እስራኤላውያን ኤላምን ሊያውቋት ቢችሉም ፋርስን ላያውቋት ይችላሉ። ይህም ኢሳይያስ ፋርስ ከማለት ይልቅ ኤላም የሚለውን ስም ለመጠቀም የመረጠበትን ምክንያት እንድንረዳ ያስችለን ይሆናል።