የግርጌ ማስታወሻ
c “ተመታ” ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል ከሥጋ ደዌ ጋር በተያያዘም ይሠራበታል። (2 ነገሥት 15:5 አ.መ.ት ) ምሁራን እንደሚሉት አንዳንድ አይሁዳውያን መሲሑ በሥጋ ደዌ ይመታል የሚለውን አስተሳሰብ ያመነጩት በኢሳይያስ 53:4 ላይ ተመርኩዘው ነው። የባቢሎናውያን ታልሙድ ይህን ጥቅስ መሲሑን ለማመልከት የተጠቀመበት ሲሆን “በሥጋ ደዌ የተያዘው ምሁር” ሲል ጠርቶታል። ዱዌይ ቨርሽን የተባለው የካቶሊክ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም በላቲኑ ቩልጌት ላይ የሰፈረውን ሐሳብ በማንጸባረቅ ይህን ጥቅስ “በሥጋ ደዌ እንደተያዘ አድርገን ቆጠርነው” ሲል ተርጉሞታል።