የግርጌ ማስታወሻ
a ‘አባት የሌለው ልጅ’ የሚለው መግለጫ ለሴቶች ልጆችም እንደሚሠራ የታወቀ ነው። ስለ ሰለጰአድ ሴቶች ልጆች የሚናገረው የመጽሐፍ ቅዱስ ዘገባ ይሖዋ፣ አባት ለሌላቸው ሴቶች ልጆችም በጥልቅ እንደሚያስብ ያሳያል። ሰለጰአድ የሞተው ወንድ ልጅ ሳይወልድ ነበር፤ በመሆኑም ይሖዋ፣ የሰለጰአድ ሴቶች ልጆች የአባታቸውን ርስት እንዲወርሱ ውሳኔ አስተላለፈ። በተጨማሪም ይህ ውሳኔ አባት የሌላቸውን ሴቶች ልጆች ሁሉ መብት የሚያስከብር ሕግ ሆኖ እንዲጸና አደረገ።—ዘኁልቁ 27:1-8